Amhara

ኢትዮጵያ በእርዳታ ስርጭት ላለመሳተፍ መስማማቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በእርዳታ ስርጭት ላለመሳተፍ መስማማቷ ተገለጸ

በኢትዮጵያ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ካሳለፍነው ግንቦት ወር ጀምሮ የመጋዝን ስርቆት ተፈጽሞብናል በሚል እርዳታ መስጠት አቁመው ነበር፡፡ እርዳታ መቆሙን ተከትሎም ስደተኞች እና የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ረሀብን ጨምሮ ተረጂዎች ህይወታቸውን እስከማጣት መድረሳቸው በተደጋጋሚ ሲገለጽ ቆይቷል፡፡ በእርዳታ እህል ስርቆቱ ላይ የፌደራል እና የክልል መንግስታት ባለስልጣናት እጃቸው እንዳለበት በወቅቱ በረድኤት ድርጅቶቹ በኩል ተገልጾም ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ለተረጂዎች የተቀመጠን እህል ወደ ጎረቤት ሀገር ይላክ እንደነበርም የተገለጸ ሲሆን የፌደራል መንግስት በወቅቱ የቀረበበትን ክስ ውድቅ አድርጓል፡፡ የአሜሪካ የልማት ተራድዖ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) ዛሬ ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ ያቋረጠውን የምግብ እርዳታ ዳግም ለማስጀመር መወሰኑን አስታውቋል፡፡ እርዳታው የተጀመረው የኢትዮጵያ መንግስት ከእርዳታው ጋር በተያያዘ በስርጭቱ ላይ እጁን እንደማያስገባ ከተስማማ በኋላ…
Read More
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ እየተባባሰ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳሳሰበው ገለጸ

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ እየተባባሰ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳሳሰበው ገለጸ

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ እየተባባሳ ነው ያለው ወንጀልና የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳስጨነቀው ተናግሯል። የህብረቱ ከፍተኛ ተወካይ ጆሴፍ ቦሬል የኢትዮጵያ መንግስት አፋጣን እርምጃ መውሰድ አለበት ብለዋል። ፍትህና ተጠያቂነት የህብረቱና የኢትዮጵያ ግንኙነት ቀስ እያለ ወደ መደበኛነት ለሚመጣው ግንኙነት ሁኔታዎች ናቸውም ሲሉ ሀሳባቸውን በቀድሞው ትዊተር በአሁኑ ኤክስ ገልጸዋል። ከሰሞኑን በተመድ ጠቅላላ ጉባኤ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ሁኔታ የቀረበ ሲሆን፤ ሀገሪቱ ከፍተኛ ክስ ቀርቦባታል። በተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት የተቋቋመው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የኢትዮጵያ መሪማሪ ሪፖርቱን አቅርቧል። የመርማሪ ቡድኑ ባለሞያ የሆኑት መሀመድ ቻንዴ ኦቶማን ባለፈው ዓመት ለተመድ የሰብዓዊ ምክር ቤት የኢትዮጵያን ሁኔታ ከገለጽን ወዲህ ሰብዓዊ መብት በሀገሪቱ በእጅጉ ተባብሶ ቀጥሏል ብለዋል። በትግራይ ክልል…
Read More
በአማራ ክልል አራት ሚሊዮን ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት አለመመለሳቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል አራት ሚሊዮን ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት አለመመለሳቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ለ2016 የትምህርት ዘመን 3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ገደማ ተማሪዎች እስካሁን አልተመዘገቡም ተባለ በአማራ ክልል ለ2016 የትምህርት ዘመን ይመዘገባሉ ተብሎ ከተያዘው ከ6 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች መካከል እስከ  ሰኞ መስከረም 07/2016 ድረስ የተመዘገቡት ተማሪዎች ቁጥር 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብቻ መሆኑን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ገልጿል፡፡ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጌታቸው ቢያዝን፤ ለ2016 የትምህርት ዘመን ከነሐሴ 23/2015 ጀምሮ እየተካሄደ ባለው የተማሪዎች ምዝገባ እስከ ሰኞ ድረስ የተመዘገቡት ተማሪዎች 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ተማሪዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። የተማሪዎችን የምዝገባ ጊዜ እስከ ሚቀጥለው ሳምንት ድረስ ነው ያሉት ኃላፊው “በተያዘው ዓመት ከ6 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዝገብ በእቅድ ተይዞ…
Read More
በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ የታሰሩ ሰዎች ህይወት በተስቦ በሽታ ማለፉ ተረጋገጠ

በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ የታሰሩ ሰዎች ህይወት በተስቦ በሽታ ማለፉ ተረጋገጠ

190 እስረኞች ታመው ህክምና ሲወስዱ ሶስት ሰዎች ደግሞ በጽኑ ህክምና ክትትል ውስጥ መሆነቸውን ኢሰመኮ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ወይም ኢሰመኮ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ አስተዳድር ስር ባለ ሲዳሞ አዋሽ የታሰሩ ሰዎችን አስመልክቶ ያደረገውን ሪፖርት ይፋ አድርጓል። ኮሚሽኑ ነሐሴ 24 እንዲሁም በጳጉሜን 2 እና 3 ቀን 2015 ዓ.ም. በዚህ ማቆያ ማእከል/ቦታ ባደረገው ጉብኝት እንዲሁም፣ በማቆያ ማእከሉ የሚገኙ ሰዎችን እና የአዲስ አበባ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮን ጨምሮ የሚመለከታቸውን የመንግሥት የጸጥታ አካላት በማነጋገር ክትትል አካሂጃለሁ ብሏል። በተጨማሪም የማቆያ ማእከሉ አስተባባሪዎች እና ጥበቃ ሲያደርጉ የነበሩ የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላትን፣ በቦታው የሕክምና አገልግሎት የሚሰጡ የሕክምና ባለሞያዎችን እና ተጨማሪ የሕክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኝ የነበረውን የጥሩነሽ ቤጂንግ ሆስፒታል ኃላፊዎችን እና ባለሞያዎችን በማነጋገር…
Read More
ተመድ ኢትዮጵያ ወደ ሀገር አቀፍ ግጭት እያመራች ነዉ ሲል አስጠነቀቀ

ተመድ ኢትዮጵያ ወደ ሀገር አቀፍ ግጭት እያመራች ነዉ ሲል አስጠነቀቀ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ኢትዮጵያ ወደ ሀገር አቀፍ ግጭት እያመራች ነዉ ሲል አሳዉቋል። በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል ያለዉም ግጭት ተበራክቷል ያለው ተመድ የግጭቶች መበራከት ኢትዮጵያን ወደ ሀገር አቀፍ መጠነ ሰፊ ግጭት ሊወስዳት ይችላል ሲልም አስጠንቅቋል። ከዚህ በተጨማሪም በአማራ ክልል ያለዉን ወቅታዊ ሁኔታ በማስመልከት ፤ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የጅምላ እስር እና እንግልት እየተፈጸመ እንደሆነም አስታውቋል። ድርጅቱ በመግለጫው አክሎም በክልሉ ፤ በመንግስት ቢያንስ አንድ ጊዜ የሰዉ አልባ አዉሮፕላን ጥቃት መፈጸሙን የደረሱኝ ሪፖርቶች ያመለክታሉ ሲልም ጠቅሷል። በአማራ ክልል በርከታ ከተሞችም ከሲቪል አስተዳደር ዉጪ በመሆን በወታደራዊ ስርዓት ስር ወድቀዋል ተብሏል። በአማራ ክልል የተፈጠረውን ጦርነት ተከይሎ ካሳለፍነው ሀምሌ ወር ጀምሮ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መደንገጉን ተከትሎ…
Read More
በአማራ ክልል ንጹሀን ዜጎች ከፍርድ ውጪ እየተገደሉ መሆኑን ኢሰመኮ ገለጸ

በአማራ ክልል ንጹሀን ዜጎች ከፍርድ ውጪ እየተገደሉ መሆኑን ኢሰመኮ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከሚያዝያ ወር 2015 ጀምሮ በአማራ ክልል የሚታየውን የጸጥታ ችግር እንዳሉ አስታውቋል። ኮሚሽኑ እንዳለው በክልሉ የነበረው የጸጥታ ችግሩ ወደ ትጥቅ ግጭት ማምራቱን ተከትሎ የንጹሀን ዜጎች ግድያ እና እንግልት ቀጥሏል ብሏል። በተለይም ከነሐሴ 19 እስከ ነሐሴ 30/2015 ድረስ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በርካታ ንጹሃን መሞታቸውን እና ለአካል ጉዳት መዳረጋቸውን ኢሰመኮ በመግለጫው አስታውቋል። "በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረማርቆስ ከተማ፣ በሰሜን ጎጃም ዞን አዴትና መራዊ፣ በደቡብ ጎንደር ዞን ደብረ ታቦር፣ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ደልጊ፣ በሰሜን ሸዋ ዞን ማጀቴ፣ ሸዋ ሮቢት እና አንጾኪያ ከተሞች እና በአካባቢዎቻቸው በሚገኙ አንዳንድ የገጠር ቀበሌዎች በግጭቱ በርካታ ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል ተብላል። እንዲሁም ለአካል ጉዳት እና የንብረት…
Read More
ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን መታሰሩ ተገለጸ

ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን መታሰሩ ተገለጸ

የትርታ ኤፍ  ኤም መስራች ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን በፌደራል ፖሊሶች ተይዞ መወሰዱን ባለቤቱ ገልፃለች። ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን ዛሬ ምሳ ሰዓት ላይ ባልዳራስ ኮንዶሚኒየም ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ በፌደራል ፖሊስ አባላት ተይዞ  ሜክሲኮ የቀድሞው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ወደሚገኘው ጊዜያዊ ማቆያ ቦታ መወሰዱን ባለቤቷ ገልፃለች ። ባለቤቱ የታሰረበት ቦታ ሄዳ የጠየቀች ሲሆን በምን ምክንያት እንደታሰረ እንዳላወቀና ለጥያቄም እንዳልቀረበ አሳውቋታል ። ጋዜጠኛ የኋላሸት ትኩረቱን በኪነ ጥበባዊ ጉዳዮች ላይ ያደረገው ኪነ ብስራት የተሰኘ የሬድዮ ሾው ለዓመታት በብስራት ኤፍ ኤም 101.1 በማቅረብ ይታወቃል። ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች ጥበቃ ቡድን ወይም ሲፒጂ ከቀናት በፊት ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ የጋዜጠኞች እስር መቀጠሉን እና የታሰሩት እንዲፈቱ ማሳሰቡ ይታወሳል።
Read More
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ አራዘመች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ አራዘመች

አሜሪካ ከሁለት ዓመት በፊት የተቀሰቃሰው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የአሜሪካንን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ይጎዳል በሚል ነበር ጦርነቱ እንዲቆም ጫና ስታደርግ የቆየችው፡፡ ይህ ጦርነት ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ምስራቅ አፍሪካን ይጎዳል የምትለው አሜሪካ ጦርነቱ እንዲቆም የተለያዩ ጫናዎችን ያደረገች ሲሆን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተፈጽሟል በሚል የተለያዩ እርምጃዎችን ስትወስድ ቆይታለች፡፡ በዋሸንግተን ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል በኢትዮጵያ ላይ ብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ ማዕቀብ የሚባል ሲሆን በፈረንጆቹ መስከረም 2021 ላይ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ማዕቀብ ተጥሏል፡፡ ይህ ማዕቀብ ከአንድ ሳምንት በኋላ የሚጠናቀቅ ቢሆንም ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ማዕቀቡ ለተጨማሪ አንድ ዓመት እንዲራዘም መፈረማቸውን አስታውቀዋል፡፡ አሜሪካ ማዕቀቡን ለአንድ ዓመት ያራዘመችው በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ አሁንም ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለምስራቅ አፍሪካ እና ለአሜሪካ የውጭ ጉዳዮች ፖሊሲ…
Read More
በአማራ ክልል በአንድ ቀን ብቻ ከ49 በላይ ንጹሃን ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል በአንድ ቀን ብቻ ከ49 በላይ ንጹሃን ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ከትናንት በስቲያ ሰኞ ነሐሴ 29 ቀን 2015 የመንግሥት የጸጥታ አካላት በወሰዱት እርምጃ እንዲሁም በድሮን ጥቃት ከ49 በላይ ንጹሃን መገደላቸውን እናት ፓርቲ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ፓርቲው በመግለጫው ሰኞ ነሐሴ 29 ቀን 2015 በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ማጀቴ ከተማ የመንግሥት ወታደሮች በወሰዱት እርምጃ 29 ንጹሃን ዜጎች በየመኖሪያ ቤታቸው በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ብሏል፡፡ "ከሟቾች ውስጥም ሕጻናት፣ ወጣቶች እና አረጋውያን እንዳሉበት ከመረጃ ምንጮቻችን አረጋግጠናል።" ያለው ፓርቲው  "በተመሳሳይ ነሐሴ 29 ቀን 2015 በምስራቅ ጎጃም ዞን ቢቡኝ ወረዳ፣ ሞሰባ ሽሜ አቦ ቀበሌ አዳራሽ ጎጥ ላይ መንግሥት በፈጸመው የድሮን ጥቃት ከ11 በላይ ንጹሐን ዜጎች ተጨፍጭፈዋል።" ብሏል። በዚሁ ቀን በምዕራብ ጎጃም ዞን ደጋ ዳሞት ወረዳ…
Read More
በኢትዮጵያ ከ4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መፈናቀላቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከ4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መፈናቀላቸው ተገለጸ

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ተቋም (IOM) ከባለፈው ሕዳር እስከ ሰኔ ወር ድረስ በ3 ሺሕ 300 መጠለያ ጣቢያዎች ሰበሰብኩት ባለው መረጃ፤ በኢትዮጵያ ከ11 ክልሎች ከ4 ነጥብ 38 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ተፈናቅለዋል ብሏል፡፡ ከነዚህ ተፈናቃዮች 66 በመቶ የሚሆኑት በግጭት ምክንያት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን ቀሪዎቹ በድርቅ እና በማህበራዊ ችግሮች ምክንያት መፈናቀላቸው ተገልጿል፡፡ሶማሌ ክልል በድርቅ ምክንያት የተፈናቀሉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች መገኛ መሆኑ ሲገለጽ፤ ትግራይ፣ አማራ ፣ኦሮሚያ እና አፋር ክልሎች በግጭት የተፈናቀሉ ዜጎች ያሉባቸው አካባቢዎች ናቸው ተብሏል፡፡ በተመሳሳይ በ10 ክልሎች ተፈናቃዮችን ለመመለስ በተደረገ ጥናት 3 ነጥብ 24 ሚሊዮን ተፈናቃዮች ወደ ቦታቸው መመለስ ይችላሉ በሚል መለየታቸውም ተገልጿል፡፡ተቋሙ አክሎም በአገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተፈናቃዮች የተመለሱባቸው…
Read More