አካባቢ ጥበቃ

ኢትዮጵያ ከቡና ንግድ ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ከቡና ንግድ ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገራት ከተላከ የቡና ንግድ በታሪክ ከፍተኛ የተባለዉን ገቢ ማግኘቷን አስታውቃለች፡፡ ኢትዮጵያ ከቡና ወጪ ንግድ በዘንድሮው በጀት አመት ከአንድ ነጥብ 4 ቢሊዮን  ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበላ እንደገለፁት ኢትዮጵያ በ2016 በጀት አመት ከቡና ሽያጭ በመጠንም ሆነ በገቢ ከፍተኛ የሆነ ውጤት አስመዝግባለች ብለዋል። ኢትዮጵያ በተያዘው በጀት ዓመት 298 ሺህ 500  ቶን ቡና ለውጪ ገበያ አቅርባ 1 ነጥብ 43 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታለች። ይህም ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በመጠንም ሆነ በገቢ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበበት እንደሆነ ዋና ዳይሬክተሩ  ጨምረው ገልፀዋል። የተላከው የቡና መጠን በ20 በመቶ እንዲሁም በዋጋ ደረጃም…
Read More
ኢትዮጵያ ከአበባ ንግድ ከ300 ሚሊዮን  ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ከአበባ ንግድ ከ300 ሚሊዮን  ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ባለፋት አስር ወራት ከአበባ ኤክስፓርት ከ 3 መቶ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች፡፡ የሆርቲካልቸር ኢንቨስትመንት ዘርፍ በተለይም የአበባ ኤክስፖርት ለኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ግኝት ከፍተኛ አስተዋጽኦን  እያበረከተ እንደሚገኝ የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል። በግብርና ሚኒስቴር የግብርና ኢንቨስትመንት እና ምርት ግብይት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ አበበ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ባለፋት አስር ወራት 79 ሺህ 819 ቶን የአበባ ምርት ለውጪ ገበያ በማቅረብ 392 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ አግኝታለች ብለዋል። የኢትዮጵያ የአበባ ምርት በአብዛኛው ወደ አውሮፓና ኤዥያ ሀገራት እንደሚላክ  የተናገሩት   ስራ አስፈፃሚው  ምርጥ አስር ተብለው ከተለዩት ተቀባይ ሀገራት መካከል ደግሞ ኔዘርላንድ ትልቁን ድርሻ ትይዛለች ብለዋል።  በበጀት አመቱ አስር ወራት ከእቅድ አፈፃፀም አንጻር ሲታይ የተገኘው ገቢ…
Read More
በኢትዮጵያ በቀጣዮቹ 10 ቀናት ከባድ ዝናብ እንደሚጠጥል ተነገረ

በኢትዮጵያ በቀጣዮቹ 10 ቀናት ከባድ ዝናብ እንደሚጠጥል ተነገረ

የኢትዮጰያ ሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት እንዳስታወቀው በቀጣዮቹ አሥር ቀናት ውስጥ ዝናብ ሰጭ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች እንደሚያመላክቱን በተለይም በመጀመሪያዎቹ ቀናት ሰፊ ቦታዎችን ያካተተና የተጠናከረ ዝናብ እንደሚኖር የትንበያ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡ በመጠንም ሆነ በሥርጭት የተስፋፋ ዝናብ የሚኖር ሲሆን እርጥበታማ የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብና በሰሜን ምዕራብ የኢትዮጲያ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸውም ኢንስቲትዩቱ ገልጿል፡፡ በአጠቃላይ በሚቀጥሉት ቀናት ከኦሮሚያ ክልል ምስራቅ እና ምዕራብ ወለጋ፣ ቄለም ወለጋ፣ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ፣ ቡኖ በደሌ፣ ጅማ፣ ኢሉባቦር፣ ቦረና እና ምስራቅ ቦረና፤ ጉጂ እና ምዕራብ ጉጂ፣ ባሌ፤ ነአማራ ክልል ሰሜን፣ ማዕከላዊ፣ ደቡብ እና ምዕራብ ጎንደር፣ ምስራቅ እና ምዕራብ ጎጃም እና አዊ ዞኖችን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች …
Read More
ኢትዮጵያ ለሕጋዊ የዱር እንስሳት አደን እስከ 15 ሺህ ዶላር እያስከፈለች መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ ለሕጋዊ የዱር እንስሳት አደን እስከ 15 ሺህ ዶላር እያስከፈለች መሆኗን ገለጸች

የዱር እንስሳትን ማደን የሚፈልጉ ጎብኚዎች በመላው ዓለም ያሉ ሲሆን አፍሪካ ዋነኛ የዱር እንስሳት አዳኞች መዳረሻ ናት፡፡ ናሚቢያ፣ ዚምባብዌ፣ ሞዛምቢክ እና ደቡብ አፍሪካ ዋነኛ የዱር እንስሳት ማደንን በሚፈልጉ ጎብኚዎች የሚጥለቀለቁ ሀገራት ናቸው፡፡ ኢትዮጵያም የዱር እንስሳትን ለህጋዊ አደን ከሚያዘጋጁ ሀገራት መካከል አንዷ ስትሆን ለዚህ የሚረዳ አሰራር መዘርጋቷን የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ልማት እና ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡ በባለስልጣኑ የዱር እንስሳት አጠቃቀም ዴስክ ሀላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ወርቁ ለአል ዔን እንዳሉት ኢትዮጵያ በአራት ክልሎች ሕጋዊ የዱር እንስሳት አደን በማካሄድ ላይ መሆኗን ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በተለይም በኦሮሚያ፣ አፋር፣ ሶማሊ እና ደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች ክምላው ዓለም ለሚመጡ ጎብኚዎች ሕጋዊ የዱር እንስሳት አደን እየተካሄደ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ለሕጋዊ አደን የተፈቀዱ…
Read More
በኢትዮጵያ በጎርፍ አደጋ አንድ ሚሊዮን ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ በጎርፍ አደጋ አንድ ሚሊዮን ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ በጎርፍ አደጋ ምክንያት አንድ ሚሊዮን የሚሆኑ ሠዎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ገለጸ ኢትዮጵያ ካሏት ሦስት ወቅቶች ውስጥ አንዱ የሆነውና አራት ወራትን የሚይዘው የበልግ ወቅት በደቡብ አጋማሽ ለሚገኙ የአገሪቱ አካባቢዎች ዋነኛ የዝናብ ወቅት ነው። ከየካቲት እስከ ግንቦት ያሉትን ወራቶችን በሚሸፍነው የበልግ ወቅት ለሶማሌ፣ ጉጂ፣ ቦረና፣ ሲዳማ፣ ደቡብ ኢትዮጵያና ለደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ ክፍሎች 55 በመቶ የዝናብ ስርጭታቸውን በዚህ ወቅት ያገኛሉ። የበልግ ወቅት ለምስራቅና ደቡብ ትግራይ፣ ለሰሜንና ደቡብ ወሎ ዞኖች፣ ለአማራና ኦሮሚያ ሰሜን ሸዋ ዞኖች፣ እንዲሁም አዲስ አበባን ጨምሮ ለመካከለኛው የአገሪቱ አካባቢ፣ ለምስራቅ አካባቢዎች (ሀረርና ድሬዳዋ) ሁለተኛ የዝናብ ወቅት ተደርጎ ይወሰዳል። የኢትዮጵያ ሚትዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የ2016 ዓ.ም. የበልግ ወቅት በተለይም ዋነኛና…
Read More
በአፍሪካ በየአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በየ ዓመቱ 250 ሺህ ሰዎች ሊሞቱ እንደሚችሉ ተገለጸ

በአፍሪካ በየአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በየ ዓመቱ 250 ሺህ ሰዎች ሊሞቱ እንደሚችሉ ተገለጸ

የፓን አፍሪካ አየር ንብረት ፍትህ ጥምረት ከዓለም ጤና ድርጅት ፣ አፍሪካ ጤና እና ጥናት ፋውንዴሽን፣ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና  ሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀት በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳቶች ዙሪያ በአዲስ አበባ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል፡፡ በዚህ መድረክ ላይ የአየር ንብረት ለውጥ ባለሙያዎች፣ የጤና ባለሙያዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና የተለያዩ ተቋማት አመራሮች ተገኝተዋል፡፡ የፓን አፍሪካ አየር ንብረት ለውጥ ፍትህ ጥምረት ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሚቲካ ምዌንዳ በመድረኩ ላይ እንዳሉት የአየር ንብረት ለውጥ ዜጎችን ለተደራራቢ የጤና ችግሮች እየዳረገ ነው ብለዋል፡፡ የአየር ንብረት ለውጥ የሰው ልጆች ለአየር ወለድ፣ ውሃ ወለድ፣ ለምግብ እጥረት እና ሌሎች የጤና ችግሮች እየዳረገ ነው ያሉት ስራ አስፈጻሚው ጉዳቱን ለመቀነስ የተቀናጀ ስራ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡…
Read More
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የገባችውን የሀይል ሽያጭ ውል ልትሰርዝ እንደምትችል ገለጸች

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የገባችውን የሀይል ሽያጭ ውል ልትሰርዝ እንደምትችል ገለጸች

ኢትዮጵያ ለሶስቱ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለሱዳን ጅቡቲ እና ኬንያ የኤሌክትሪክ ሀይል በመሸጥ ላይ ስትሆን ለተጨማሪ ሀገራትም ሀይል ለመሸጥ የአዋጭነት ጥናት በማካሄድ ለይ ትገኛለች፡፡ ከአንድ ወር በፊት በታንዛኒያ ጉብኝት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አዲ የሀይል ሽያጭ ስምምነት ተፈራርመው መመለሳቸው ይታወሳል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኬንያ ሀምሌ 2022 ላይ ለ25 ዓመት የሚዘልቅ የሀይል ሽያጭ ስምምነት የተፈራረመች ሲሆን የሀገሪቱ ፍርድ ቤት ከዚህ በፊት የተደረጉ የሀይል ሽያጭ ስምምነቶች ሳይመረመሩ ተጨማሪ ስምምነቶች እንዳይካሄዱ እገዳ ጥሏል፡፡ ፍርድ ቤቱ በኬንያ መንግስት ላይ እገዳ ጣለው በገጠር ለሚኖረው ህዝብ እየቀረበ ያለው የኤሌክትሪክ ሀይል ታሪፍ ውድ ነው በሚል ነው፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ለኬንያ ሀይል የምትሸጠው ኢትዮጵያ ከጠቅላላ ህዝቧ ውስጥ ግማሽ ያህሉ…
Read More
በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ቅጽበታዊ ጎርፍ አደጋ ሊደርስ እንደሚችል ተገለጸ

በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ቅጽበታዊ ጎርፍ አደጋ ሊደርስ እንደሚችል ተገለጸ

በኢትዮጵያ አብዛኞቹ ቦታዎች ቀጣዮቹ ቀናት የበልግ ዝናብ በአብዛኛዎቹ የበልግ አብቃይ አካባቢዎች ላይ ይጠናከራል ተብሏል፡፡ በመጪዎቹ 10 ቀናት የበልግ ዝናብ በአብዛኛዎቹ የበልግ አብቃይ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ላይ እየተጠናከረና እየተስፋፋ እንደሚሄድ የኢትዮጵያ ሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል። ይህን ተከትሎም በበልግ አብቃይ አካባቢዎች በርካታ ቦታዎቻቸውን የሚሸፍን ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም አስታውቋል። በተጨማሪም በውሃ አካላትና በከባቢ አየር ውስጥ ከሚጠናከሩት የሚቲዮሮሎጂ ገጽታዎች ላይ በመነሳት ምስራቅ ሸዋ፣ አዲስ አበባ፣ ምስራቅ አማራ፣ ሐረር፣ ድሬዳዋ እና አይሻ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ጠቅሷል። ከኦሮሚያ ክልል የቄለም ወለጋ፣ የምዕራብ ወለጋ፣ ቡኖ በደሌ፣ ኢሉአባቦር፣ ጅማ፣ ሁሉም የሸዋ ዞኖች፣ አርሲና ምዕራብ አርሲ፣ ባሌና ምስራቅ…
Read More
ኢትዮጵያ ከሚያዚያ ጀምሮ የነዳጅ ድጎማ እንደምታነሳ ገለጸች

ኢትዮጵያ ከሚያዚያ ጀምሮ የነዳጅ ድጎማ እንደምታነሳ ገለጸች

ኢትዮጵያ የየነዳጅ ፍላጎቷን ሙሉ ለሙሉ ከውጭ ሀገራት በመግዛት የምትሸፍን ሲሆን የትራንስፖርት ዋጋ እንዳያንር በሚል የነዳጅ ድጎማ ስታደርግ ቆይታለች፡፡ የመንግስት ወጪ በመጨመሩ እና የገንዘብ እጥረት በማጋጠሙ ምክንያት የነዳጅ ድጎማን ቀስ በቀስ ለመቀነስ እና ለማቆም እንደወሰነች የትራንስፖርት ሚኒስቴር ባሳለፍነው ዓመት ይፋ አድርጓል፡፡ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ለማይሰጡ ድርጅቶች የነዳጅ ድጎማው ከቆመ አንድ ዓመት ያለፈው ሲሆን አሁን ደግሞ የህዝብ ትራንስፖርት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎችም የነዳጅ ድጎማ እንደማያገኙ ተገልጿል፡፡ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የነዳጅ ድጎማ ሲደረግላቸው የነበሩ የሚኒባስ ተሽከርካሪዎች ከመጋቢት 30 ቀን  2016 ዓ.ም ጀምሮ ድጎማው እንደሚቋረጥ የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታውቋል። መንግሥት ለረጅም ጊዜ ለነዳጅ ምርቶች ከፍተኛ መጠን የለው ድጎማን ሲያደርግ መቆየቱን በመግለጽ ይህንን ለማስቀረት በሂደት የነዳጅ ምርቶች…
Read More
ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ሙሉ በሙሉ አገደች

ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ሙሉ በሙሉ አገደች

ከወራት ማመንታት በኋላ የኢትዮጵያ መንግስት በነዳጅ የሚሰሩ የግል አገልግሎት ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ እገዳ መጣሉ ተገልጿል፡፡ መኪኖችን ከተለያዩ ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ በማስመጣት ስራ የተሰማሩ ኩባንያዎች እንዳሉት ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ማስገባት እንደማይችሉ እንደተነገራቸው ተናግረዋል። ከመካከለኛው ምስራቅ፣ ከአውሮፓና ደቡብ አፍሪቃ ያጓጓዟቸውን በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ማስገባት እንደማይችሉ ከሶስት ሳምንት በፊት ተነግሯቸዋል። በእገዳው ሳቢያ ከፍተኛ መጉላላትና ኪሳራ እንደደረሰባቸው ባለጉዳዮቹ ለሪፖርተር ጋዜጣ ተናግረዋል። ከሳምንታት በፊት የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ማገዱን ለፓርላማ አባላት ሲያስታውቅ የገንዘብ ሚኒስቴር በበኩሉ እገዳው ተገባራዊ እንደማይደረግና በዕቅድ ደረጃ ያለ መሆኑን ተናግሮ ነበር። ይሁንና ባለፉት ቀናት የተለየ ፍላጎት ላላቸው የልማት ፕሮጀክቶችና ለህዝብ ትራንስፖርት የሚውሉ ካልሆኑ በቀር በነዳጅ የሚሰሩ…
Read More