New admin

1105 Posts
ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ የ2023 ‹‹የዓለም አቀፍ የጀግና ሴቶች ሽልማት›› አሸነፈች

ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ የ2023 ‹‹የዓለም አቀፍ የጀግና ሴቶች ሽልማት›› አሸነፈች

ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ የ2023 ‹‹የዓለም አቀፍ የጀግና ሴቶች ሽልማት›› አሸነፈች መምህርት፣ ጋዜጠኛና አክቲቪስት መዓዛ መሐመድ የ2023 የ‹‹ዓለም አቀፍ የጀግና ሴቶች ሽልማት (International Women of Courage/IWOC Awards)›› አሸናፊ ሆናለች፡፡  ‹‹ዓለም አቀፍ የጀግና ሴቶች ሽልማት›› በመላው ዓለም ከባድ አደጋዎችንና ፈተናዎችን ተቋቁመው ሰላም፣ ፍትህ፣ ሰብዓዊ መብቶች፣ የፆታ እኩልነት እና የሴቶች ተጠቃሚነት እንዲከበሩና እንዲሰፍኑ ልዩ ጥንካሬ፣ ጀግንነትና የአመራር ጥበብ ላሳዩ ሴቶች የሚበረከት ሽልማት ነው፡፡ ሽልማቱ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚዘጋጅ ሲሆን፣ ዘንድሮ ለ17ኛ ጊዜ የሚካሄድ ይሆናል፡፡ እስካሁን ድረስም ከ80 ሀገራት የተገኙ ከ180 በላይ ጀግና ሴቶችን እውቅና ሰጥቷል፡፡ በዘንድሮው ሽልማት ከአራት አህጉራት የተገኙ 11 ጀግና ሴቶች እና አንድ የሴቶች ቡድን እውቅና ይሰጣቸዋል፡፡    ለሽልማቱ የሚመረጡት ሴቶች…
Read More
ዶናልድ ትራምፕ ቻይና 50 ትሪሊዮን ዶላር ካሳ እንድትከፍል ጠየቁ

ዶናልድ ትራምፕ ቻይና 50 ትሪሊዮን ዶላር ካሳ እንድትከፍል ጠየቁ

ዶናልድ ትራምፕ ቻይና 50 ትሪሊዮን ዶላር ካሳ እንድትከፍል ጠየቁ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቻይና 50 ትሪሊዮን ዶላር ካሳ ልትከፍል ይገባል ብለዋል። የኮሮና ቫይረስ ከቻይና ውሀን ቤተ ሙከራ ውስጥ ማምለጡን የሚናገሩት ትራምፕ ቫይረሱ በአሜሪካ ላይ ላደረሰው ጉዳት ቻይና ካሳ እንድትከፍል ጠይቀዋል ሲል ዴይሊ ሜይል ዘግቧል። አሜሪካ በተደጋጋሚ የኮሮና ቫይረስ ከቻይና ቤተ ሙከራ አምልጧል በሚል ስትናገር የሚሰማ ሲሆን ቻይና ግን ይህን ክስ ውድቅ አድርጋለች። የኮረና ቫይረስ በዓለም ላይ ከስድስት ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ሲገድል አሜሪካ፣ ብራዚል እና ሕንድ ብዙ ዜጎቻቸውን በሞት ያጡ ሀገራት ናቸው።
Read More
ሽመልስ አብዲሳ ከብጹአን አባቶች ጋር ስምምነት ላይ ቢደርሱም አሁንም ችግሮች እንዳልተፈቱ ተገለጸ

ሽመልስ አብዲሳ ከብጹአን አባቶች ጋር ስምምነት ላይ ቢደርሱም አሁንም ችግሮች እንዳልተፈቱ ተገለጸ

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ ከሰሞኑ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን አባቶች ጋር በወቅታዊ የቤተክርስትያን ጉዳዮች ላይ ተወያይተው ችግሮችን ለመፍታት ቃል የገቡ ቢሆንም አሁንም ችግሮች እንዳልተፈቱ ተነግሯል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ያቋቋመችው የሕግ ኮሚቴ አባል የሆኑት የሕግ ባለሙያና ጠበቃ አያሌው ቢታኔ ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት፣ ፕሬዝዳንቱ በቤተክርስያን ጉዳይ የታሰሩ ሰዎች እስከ ዛሬ ማክሰኞ ድረስ ይፈታሉ ብለው ቃል የገቡ ቢሆንም፣ ሽንገላ የሚመስል ነገር እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡ የኦሮሚያ ክልል መንግሥትና የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ሕግን የማስፈጸም ግዴታ እያለባቸው ያለባቸውን ኃላፊነት ባለመወጣታቸው ምክንያት አሁንም በርካታ የሕግ ጥሰቶችና የንብረት ውድመቶች እየደረሱ እንደሆነ ጠበቃው ተናግረዋል፡፡ ትናንት ሰኞ በፍርድ ቤት እግድ የተጣለባቸውና ከቤተክርስትያኗ ቀኖና ውጭ የተሾሙ ግለሰቦች በአሰላ የአቡነ…
Read More
ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በሟቋረጧ ብቻ 146 ሚሊየን ዶላር ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በሟቋረጧ ብቻ 146 ሚሊየን ዶላር ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጥ ብቻ 146 ሚሊየን ዶላር ማጣቷ ተነገረ ቶፕ 10 ቪፒኤን የቴክኖሎጂ ኩባንያ እንዳስታወቀው፣ በትግራይ ክልል የነበረውን ጦርነት ተከትሎ ለአንድ አመት ሙሉ የኢንተርኔት አገልግሎት በመዘጋቱ ሃገሪቱ 146 ሚሊዮን ዶላር ማጣቷን አስታውቋል። አሁንም ቢሆንም በመላው ሀገሪቱ ኢንተርኔት በመቋረጡ ሚሊዮን ዶላሮችን እያጣች ትገኛለች ብሏል። ኢንተርኔት ከተዘጋ ዛሬ 28ኛ ቀኑን የያዙ ሲሆን መንግሥት እስካሁን ስለጉዳዩ ያለው ነገር የለም። መንግሥት የዘጋውን የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲከፍት የተሉያዩ አካላት ግፊት በማድረግ ላይ ሲሆኑ የኢትዮጵያ ሚዲያ ምክር ቤት እና ኢሰመኮ ከሰሞኑ ኢንተርኔት እንዲለቀቅ ከጠየቁ ተቋማት መካከል ዋነኞቹ ናቸው። ኢትዮጵያ በዓለም ላይ የኢንተርኔት አገልግሎት እቀባ ከሚፈጽሙ ሀገራት መካከል አንዷ እንደሆነች ኔትብሎክስ ከዚህ በፊት ባወጣው ሪፖርት ገልጿል። ቲክቶክ፣ዩቲዩብ፣ቴሌግራም…
Read More
ኡጋንዳውያን የዓለም ፍጻሜ ደርሷል በሚል ወደ ኢትዮጵያ መፍለሳቸው ተገለጸ

ኡጋንዳውያን የዓለም ፍጻሜ ደርሷል በሚል ወደ ኢትዮጵያ መፍለሳቸው ተገለጸ

በመቶዎች የሚቆጠሩ የኡጋንዳ የሐይማኖት ኑፋቄ አባላት የምፅዓት ቀንን በመስጋት ወደ ኢትዮጵያ እየተሰደዱ ነው ተብሏል፡፡ የኑፋቄ መሪዎቹ የዓለም መጨረሻ እንደቀረበና ሞትም አካባቢያቸውን እንደሚመታ አሳምኗቸዋል። በኡጋንዳ ምስራቃዊ ክፍል ውስጥ የሚገኙ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከቀያቸው ወደ ኢትዮጵያ መሰደዳቸውን የኡጋንዳ ፖሊስ አስታወቋል። ፖሊስ ባደረገው ምርመራ የኑፋቄው አባላት ከአካባቢያቸው ይጀመራል ብለው ካመኑበት የዓለም ፍጻሜ ለማምለጥ ሸሽተዋል ብሏል። የኑፋቄው አባላት በቅርቡ አካባቢያቸው በሞት እንደሚመታ እና ሁሉም ሰዎች እንደሚሞቱ በመሪዎቹ እንደተነገራቸው ገልፀዋል። ንብረታቸውን ሸጠው ወደ ኢትዮጵያ መሰደዳቸው የተነገረው አነዚህ ኡጋንዳውያን ከዚያም ካሉበት በኡጋንዳ ከሚገኙ አንዳንድ ዘመዶቻቸው ጋር እየተነጋገሩ ነው። “የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ቤተክርስቲያን በሚባል የሃይማኖት ኑፋቄ ላይ በኡጋንዳ ምስራቃዊ ሴሬሬ ወረዳ በኦቡሉም መንደር ውስጥ የሚገኘውን የሃይማኖት ክፍል…
Read More
በኢትዮጵያ የኩላሊት እጥበት በሚያደርጉ ህሙማን ላይ 50 በመቶ የዋጋ ጭማሪ ተደረገ

በኢትዮጵያ የኩላሊት እጥበት በሚያደርጉ ህሙማን ላይ 50 በመቶ የዋጋ ጭማሪ ተደረገ

በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣው የኩላሊት ህሙማን ቁጥር በርካቶችን ለችግር እየዳረገ እንደሚገኝ ተጠቁሟል ። የህሙማኑን አቅም እየፈተነ የሚገኘው አቅምን ያላገናዘበ የህክምና ወጪ የብዙዎችን ቤት እያንኳኳ ይገኛል ሲሉ የኩላሊት ህመምተኞች እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን አሰፋ ተናግረዋል። በአሁኑ ሰዓት በዳግማዊ ሚኒሊክ ፣ በዘውዲቱ እና በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታሎች 180 ህሙማን የነፃ ህክምና አገልግሎት እየተጠቀሙ ቢሆን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ህሙማን ዕድሉን ባለማግኘታቸው ችግር ላይ መውደቃቸውን አቶ ሰለሞን ጠቁመዋል። እነዚህ ህሙማን ከእዚህ ቀደም በግል የህክምና ተቋማት ለአንድ ጊዜ የኩላሊት እጥበት ይጠየቁ ከነበረው ክፍያ እስከ 50 ከመቶ ጭማሪ እንደተደረገባቸው ስራ አስኪያጁ ያነሱ ሲሆን በግል የህክምና ተቋማት ለአንድ ጊዜ እጥበት ይጠይቅ…
Read More
ኢትዮጵያ 500 ሺህ ሴቶችን ወደ ሳውዲ አረቢያ ልትልክ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ 500 ሺህ ሴቶችን ወደ ሳውዲ አረቢያ ልትልክ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ 500 ሺሕ ሴቶችን ወደ አረብ አገር ልትልክ ነው በኢትዮጵያ በተያዘው ዓመት 500 ሺሕ ሴቶችን ወደ አረብ አገራት በተለይም ወደ ሳውዲ አረቢያ ለሥራ ለመላክ በመንግሥት እቅድ መያዙ ተገለጸ፡፡ ይህን ተከትሎም በአማራ ክልል ኹሉም ዞኖች ሰሞኑን ወደ አረብ አገር ሄደው መስራት ለሚፈልጉ ወጣት ሴቶች ስልጠና ሊሰጥ መሆኑን ኢትዮ ነጋሪ ሰምታለች፡፡ ለአብነትም በምስራቅ ጎጃም ዞን ሦስት የስልጠና ማዕከላት የተዘጋጁ ሲሆን፣ በሞጣ፣ ደብረ ማርቆስ እና ደጀን ከተሞች ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ ሴቶች የቤት አያያዝና ሌሎች አስፈላጊ የሥራ ስልጠናዎች እንደሚሰጡኢትዮ ነጋሪ ከዞኑ መረጃ አግኝታለች፡፡ ስልጠናው ለ20 ቀን በመንግሥት በነጻ የሚሰጥ መሆኑን የተገለጸ ሲሆን፤ ከስልጠናው በኋላ ፈቃደኛ የሆኑ ሴቶች ወደ ሳውዲ አረቢያ የሚያቀኑበት የዚህ…
Read More
የኢትዮጵያ አቪየሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ አደገ

የኢትዮጵያ አቪየሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ አደገ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቪዬሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ በማደግ በኤሮስፔስ እና በተለያዩ የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፎች በቅድመ ምረቃ እና ድሕረ ምረቃ ፕሮግራሞች ማስተማር ጀመረ። የአቪዬሽን አካዳሚ የአቪዬሽን ስልጠና ፕሮግራሞችን በአብራሪነት፣ የአውሮፕላን ቴክኒሻን፣ የካቢን ሰራተኛ፣ የአየር መንገድ ሽያጭ እና አገልግሎት እና ሌሎች ስልጠናዎችን ሲሰጥ ቆይቷል።  ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ ካደገ በኋላ በኤሮኖቲካል ኢንጂነሪንግ በቢኤስሲ ዲግሪ፣ በአውሮፕላን ጥገና ኢንጂነሪንግ በቢኤስሲ ዲግሪ፣ በአቪዬሽን ማኔጅመንት ቢኤስሲ ዲግሪ፣ በቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ማኔጅመንት ቢኤ ዲግሪ እና ኤምቢኤ በአቪዬሽን ማኔጅመንት የመሳሰሉ የዲግሪ መርሃ ግብሮችን ጀምሯል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው እንደተናገሩት "ከቀጣይ እድገትና ኢንቨስትመንት በኋላ 65 ዓመት ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ ማደጉ…
Read More
ዘምዘም ባንክ ከሀገር እና ውጭ ሀገራት ባንኮች ጋር ለመዋሃድ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

ዘምዘም ባንክ ከሀገር እና ውጭ ሀገራት ባንኮች ጋር ለመዋሃድ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

ዘምዘም ባንክ ከሀገር እና ውጭ ሀገራት ባንኮች ጋር ለመዋሃድ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ የኢትዮጵያ የባንክ ህግ መሻሻሉን ተከትሎ በቅርቡ ወደ አገልግሎት የገባው ዘምዘም ባንክ የተሻለ ገቢ እና ተወዳዳሪ ለመሆን ከሌሎች ባንኮች ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ የባንክ ታሪክ ሙሉ ለሙሉ የእስላሚክ ባንክ አገልግሎትን በመስጠት ቀዳሚ የሆነው ዘምዘም ባንክ ከማንኛውም የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገራት ባንኮች ጋር ተዋህዶ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን የባንኩ ፕሩዝዳንት ወይዘሮ መሊካ ለኢትዮ ነጋሪ በድሪ ተናግረዋል፡፡ ፕሬዝዳንቷ አክለውም ዘምዘም ባንክ ስራ ከጀመረበት ሰኔ 2013 ዓ.ም ጀምሮ በ54 ቅርንጫፎቹ በሀገር አቀፍ ደረጃ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ ባንኩ ሙሉ ለሙሉ ወለድ አልባ የሆኑ ሁሉንም የፋይናንስ አገለግሎቶችን በመስጠት ላይ መሆኑን የተናገሩት…
Read More
የአንድ ኪሎ ሽንኩርት ዋጋ ከሥጋ ከሁለት እጥፍ በላይ የተወደደባት አገር

የአንድ ኪሎ ሽንኩርት ዋጋ ከሥጋ ከሁለት እጥፍ በላይ የተወደደባት አገር

ለምግብ ማጣፈጫነት ከሚውሉ አትክልቶች መካከል ሽንኩርት አንዱ ነው። ሽንኩርት በዓለም ዙሪያ መሠረታዊ የምግብ ግብአቶች ከሆኑት መካከል ይጠቀሳል። በበርካታ አገራት ሽንኩርት በድሃውም ሆነ በሃብታሙም ቤት የሚገኝ የምግብ አካል ሲሆን፣ ሥጋ ደግሞ እንደ ቅንጦት ምግብ የሚታይ ነው። በፊሊፒንስ ግን ይህ በተቃራኒ ሆኗል፤ የሽንኩርት ዋጋ የትኛውንም አይነት ሥጋ ለመግዛት ከሚወጣው ገንዘብ በበርካታ እጥፍ ይበልጣል። ለፊሊፒን ዜጎች ባለፉት ሳምንታት ጊዜ ሽንኩርት መሸመት ቅንጦት ሆኗል። ዋጋው በማሻቀቡ የተነሳ የሽንኩርት መግዣ ከሥጋ መግዣ በእጅጉ ንሯል። በዚህ ሳምንት ፊሊፒንስ ውስጥ አንድ ኪሎ ሽንኩርት 11 ዶላር (600 ብር ገደማ) ሲሆን፣ የአንድ ሙሉ ዶሮ ሥጋ ግን 4 ዶላር (220 ብር ገደማ) ብቻ ነው። የሽንኩርት ዋጋ ንረት የፈጠረውን የገበያ ክፍተት…
Read More