21
Oct
መዳን የማይችሉ ሰዎችን ህይወት ማቋረጥ የሚፈቅድ ረቂቅ ህግ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቧል። በጤና ሚኒስቴር አዘጋጅነት ባሳለፍነው ሳምንት የቀረበው ይህ ረቂቅ አዋጅ "የጤና አገልግሎት አስተዳደር አዋጅ" ተብሎ ቀርቧል፡፡ በዚህ ረቂቅ አዋጅ ውስጥ በርካታ ከጤና ጋር የተያያዙ ስርዓቶች የቀረቡ ሲሆን በተፈጥሯዊ መንገድ ልጅ መውለድ ላልቻሉ ባለትዳሮች በቴክኖሎጂ የታገዘ የህክምና አገልግሎት ስለሚያገኙበት መንገድ ያስረዳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም አተነፋፈሳቸው በመሳሪያ ላይ ብቻ የተመሰረተ ሥርዓት ስለሚቋረጥበት ሁኔታ የሚደነግግ ረቂቅ ህግም ለምክር ቤቱ ቀርቦለታል፡፡ የዚህ ረቂቅ ህግ አላማም የሃገሪቱን እድገት ለማሳለጥና የህብረተሰቡን ኑሮ ለማሻሻል በሚደረግ ጥረት የልማቱ አንቀሳቃሽ የሆነውን ሕዝብ ጤንነት በተሟላ ሁኔታ መጠበቅ እንደሆነ ተጠቅሷል። በዚህ ረቂቅ ህግ መሰረት በመሳሪያ ላይ ብቻ የተመሰረተ የአተነፋፈስ ስርዓትን…