Business

ለኢትዮ ጅቡቲ ባቡር መስመር አዲስ ሀላፊ ተሾመለት

ለኢትዮ ጅቡቲ ባቡር መስመር አዲስ ሀላፊ ተሾመለት

ዳንኤል ኃ/ሚካኤል የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር ዋና ስራ አስፈፃሚ ተደርገው ተሾመዋል፡፡ የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር (ኢዲአር) ቺፍ ቴክኒካል ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት ኢንጂነር ዳንኤል ኃ/ሚካኤል ከሰኔ 21 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ተጠባባቂ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነዉ ተሾመዋል። የኢትዮ ጂቡቲ ባቡር የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ ለኢትዮ ጂቡቲ ባቡር አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ በነበሩት አብዲ ዘነበ ምትክ ዳንኤልን ኃ/ሚካኤልን ተጠባባቂ ዋና ስራ አስፈፃሚ እንዲሆኑ መድበዋል። የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማኅበር ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከተጓዦችና የጭነት አገልግሎት ከ2 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱ ይታወሳል። ማኅበሩ በየቀኑ ከ700 እስከ 1 ሺህ ሰዎችን የማጓጓዝ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከ155…
Read More
ቻይና በአማርኛ ቋንቋ ያስተማረቻቻውን የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች አስመረቀች

ቻይና በአማርኛ ቋንቋ ያስተማረቻቻውን የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች አስመረቀች

ቻይና በአማርኛ ቋንቋ ያስተማረቻቻውን የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎችን በትናትናው እለት አስመርቃለች። በቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርስቲ (BFSU) በትናንትናው ዕለት ተማሪዎቹን ያስመረቀ ሲሆን፤ ከተመራቂዎቹ መካከልም በአማርኛ ቋንቋ በመጀመሪያ ዲግሪ ያስተማራቸውን ተማሪዎቹ ይገኙበታል። በቻይና የኢትዮጵያ ኤማባሲ ተወካዮች ቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርስቲ (BFSU) የአማርኛ ቋንቋ ተማሪዎች ምርቃት ላይ መሳተፋቸውንም ኤምባሲው አስታውቋል። “በቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርስቲ (BFSU በቻይና ውስጥ ብቸኛው የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ክፍል የሚሰጥ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን፤ ትናንት ከተመረቁት መካከል የመጀመሪያው ዙር የአማርኛ ተማሪዎች ይገኙበታል ብሏል ኤምባሲው ባወጣው መረጃ። ኤምባሲው ቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርስቲ የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት መስጠቱን አመስግኖ፤ “ይህ የሁለቱን ሀገራት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ያጠናክራል” ብሏል። የቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርሲቲ ለቻይናውያን ተማሪዎች የተዘጋጁ የአማርኛ መማሪያ…
Read More
ሳፋሪኮም ኬንያ የደንበኞችን መረጃ ለመንግስት አሳልፎ እንዳልሰጠ ገለጸ

ሳፋሪኮም ኬንያ የደንበኞችን መረጃ ለመንግስት አሳልፎ እንዳልሰጠ ገለጸ

ዋና መቀመጫውን ናይሮቢ ያደረገው ሳፋሪኮም ኬንያ የደንበኞቹን መረጃ ለመንግስት እንዳልሰጠ አስታውቋል፡፡ ድርጅቱ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ የአገሪቱን የመረጃ ጥበቃ ህግ መሰረት በማድረግ የደንበኞቹን ነፃነት እንደሚያከብር አስታውቋል፡፡ ተቋሙ እንዳለው በፍርድ ቤት አማካኝነት ካልታዘዘ በስተቀር ማንኛውንም የደንበኞቹን መረጃ ለሌላ ሶስተኛ አካል አሳልፎ እንደማይሰጥ ገልጿል፡፡ ድርጅቱ እስካሁን የደንበኞቹን መረጃ እንዲሰጥ ከመንግስት ጥያቄ እንዳልቀረበለት አስታውቋል፡፡ እንዲሁም የደንበኞቹን መረጃ ለመንግስት አካል አሳልፎ እንዲሰጥ የሚጠይቅ የፍርድ ቤት ትእዛዝ እንዳልደረሰውም በመግለጫው ላይ ጠቅሷል፡፡ የድርጅቱ እህት ኩባንያ የሆነው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ አጋርነት ለኢትዮጵያ በሚል ሰኔ ወር 2013 ዓ.ም ላይ በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ህጋዊ ፍቃድ ከተቀበለ ከአንድ ዓመት በኋላ ስራ መጀመሩ ይታወሳል፡፡ ከሶስት ዓመት በፊት ወደ…
Read More
በአማራ ክልል የተወሰኑ ወረዳዎች የባንክ አገልግሎት ተቋረጠ

በአማራ ክልል የተወሰኑ ወረዳዎች የባንክ አገልግሎት ተቋረጠ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የፋኖ ሀይሎች በተቆጣጠሯቸውና ወጣ ገባ በሚሉባቸው ወረዳዎች የባንክ አገልግሎት ተቋርጧል፡፡ የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ አደራጃለሁ የሚል ውሳኔ ከወሰነበት ጀምሮ በአማራ ክልል በፋኖ ታጣቂዎች እና የመንግስት የጸጥታ ሀይሎች መካከል ጦርነት ከተቀሰቀሰ አንድ ዓመት አልፎታል፡፡ በዚህ ጦርነት ምክንያት በክልሉ ለ10 ወራት የዘለቀ የአስቸኳይ አዋጅ የታወጀ ሲሆን ካሳለፍነው ሳምንት ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም ጀመሮም የአዋጁ ጊዜ ቢያበቃም ክልሉ በኮማንድ ፖስት እየተዳደረ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለም ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ በሰሜን ሸዋ ዞን የተወሰኑ ወረዳዎች የባንክ አገልግሎት ተቋርጧል፡፡ የባንክ አገልግሎት ከተቋረጠባቸው ወረዳዎች መካከል መንዝ ላሎ፣ ግሼ ራቤል፣ አንፆኪያ ገምዛ እና ቀወት ወረዳዎች እንደሚገኙበት ዋዜማ ሬዲዮ…
Read More
ለወሎ ተርሸሪ ሆስፒታል ግንባታ በሚል የተሰራጨው የ17 ሚሊዮን ብር ኩፖን መጥፋቱ ተገለጸ

ለወሎ ተርሸሪ ሆስፒታል ግንባታ በሚል የተሰራጨው የ17 ሚሊዮን ብር ኩፖን መጥፋቱ ተገለጸ

የፌደራል ዋና ኦዲተር የ2015 በጀት ዓመት የፌደራል መንግሥት ተቋማትን የበጀት ኦዲት ዋና ዋና ግኝቶችን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል። ዋና ኦዲተር በሪፖርቱ ላይ እንዳለው ከህዝብ በቀረበለት ጥያቄ መሰረት ኦዲት ካደረጋቸው ስራዎች መካከል የወሎ ተርሸሪ የህክምና እና የማስተማሪያ ሆስፒታል ግንባታ ዋነኛው ነው፡፡ በተሰራው የኦዲት ሪፖረት መሰረትም ለሆስፒታሉ ግንባታ በሚል የገቢ ማሰባሰቢያ በሀገር ውስጥ እና ውጭ ሀገራት ሲደረግ እንደነበር ተገልጿል፡፡ ለዚህም ሲባል በውጭ ሀገራት በሚገኙ የኢትዮጵያ ኢምባሲዎች እና ቆንስላ ጽህፈት ቤቶች፣ ክልሎች እና ሌሎች አካባቢዎች ይሸጣል ተብሎ 9 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ኩፖን ተሰራጭቶ እንደነበር በሪፖርቱ ላይ ተገልጿል፡፡ ይሁንና ይህ 9 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር የሚያወጣው የገቢ መሰብሰቢያ ኩፖን እንደጠፋ ተገልጿል፡፡ ከዚህ…
Read More
ማስተርካርድ ፋውንዴሽን ለ12 የኢትዮጵያ ጀማሪ ተቋማት 720 ሺህ ዶላር ድጋፍ አደረገ

ማስተርካርድ ፋውንዴሽን ለ12 የኢትዮጵያ ጀማሪ ተቋማት 720 ሺህ ዶላር ድጋፍ አደረገ

ለስምንት ሳምንታት ያህል ማመልከቻዎችን ሲቀበል ከቆየ በኋላ፣ ሪች ፎር ቼንጅ ኢትዮጵያ (Reach for Change Ethiopia) በዛሬው ዕለት የማስተርካርድን ኤድቴክ ፕሮግራም የመጀመሪያውን ዙር የተቀላቀሉትን 12 የኤድቴክ ሥራ ፈጣሪዎች ይፋ አድርጓል። “ኤድቴክ” (EdTech) በእንግሊዝኛው ትምህርት እና ቴክኖሎጂን አጣምሮ የያዘ ቃል ሲሆን፣ ትምህርትን አሳታፊ በሆነና ምቹ መንገድ ለማቅረብ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀምን የሚገልጽ ሐሳብ ነው። ፕሮግራሙ የሪች ፎር ቼንጅ እና የማስተርካርድ ፋውንዴሽን አጋርነት አንድ አካል ሲሆን፣ የአጋርነቱ ዓላማም ለተመረጡ የኤድቴክ ድርጅቶች ቁልፍ የሆነ የቢዝነስና የፋይናንስ ድጋፍ መስጠት ነው። ከዚህ በተጨማሪ፣ ፕሮግራሙ ለድርጅቶቹ አዲስን ነገር ስለ መማር ሳይንስ፣ ስለ እድገትና መስፋፋት፣ ስለ ዘላቂነት እንዲሁም ተጽዕኖ ስለ መፍጠር ምልከታን የሚያስጨብጥ ይሆናል። “እነዚህ ፕሮግራሙን የተቀላቀሉ 12 የኤድቴክ…
Read More
ሳፋሪኮም እና ገበያ ኩባንያ የኢትዮጵያን የሥራ ፈጠራ ሥነ ምህዳር የሚያሳድግ “ታለንት ክላውድ” ጀመሩ

ሳፋሪኮም እና ገበያ ኩባንያ የኢትዮጵያን የሥራ ፈጠራ ሥነ ምህዳር የሚያሳድግ “ታለንት ክላውድ” ጀመሩ

ሳፋሪኮም ከገበያ ኩባንያ ጋር በአጋርነት፣ እንዲሁም የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (JICA) ድጋፍ ታክሎበት “ሳፋሪኮም ታለንት ክላውድ” የተሰኘ ፕሮግራም ይፋ አድርገዋል። ፕሮግራሙ የመረጃ መረብን በመጠቀም የሥራ ዕድልን የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል። ፕሮግራሙ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነና ቀጣዩን የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች፣ ሥራ ፈጣሪዎች እንዲሁም የዲጅታሉ ዓለም መሪዎችን አቅም ለማሳደግ ያለመ ነው። ይህ የተለየ አሠራርን ይዞ የመጣው ፕላትፎርም እስከ 2024 እ.ኤ.አ ማብቂያ ድረስ፣ ለ10 ሺሕ ልዩ ልዩ ክህሎት ያላቸው ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች አጠቃላይ የአቅም ግንባታ እንዲሁም የሥራ ጉዟቸውን ማሳደጊያ ዕድሎችን የሚያቀርብ ነው። ይህንን በማድረግ፣ በአገሪቱ ውስጥ የሚስተዋለውን የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂውን ኢንዱስትሪ ዕድገት የገታውን የቴክኖሎጂ ክህሎት እጥረት ለመቅረፍ ፕሮግራሙ ዒላማ ያደርጋል። "የሳፋሪኮም ታለንት ክላውድ “ለመጪው ዲጂታል ዘመን የኢትዮጵያንን…
Read More
ዳሸን ባንክ ለሶስተኛ ጊዜ የዳሸን ከፍታ የስራ ፈጠራ ውድድርን ሊጀምር ነው                                                                                 

ዳሸን ባንክ ለሶስተኛ ጊዜ የዳሸን ከፍታ የስራ ፈጠራ ውድድርን ሊጀምር ነው                                                                                 

ዳሸን ባንክ በስራ ፈጠራ ዘርፍ የበኩሉን አስተዋፅኦ ለማበርከት እየተገበረ ያለው ዳሸን ከፍታ የስራ ፈጠራ ውድድር ለሶስተኛ ጊዜ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ይካሄዳል፡፡ ባንኩ ውድድሩን ስኬታማ በሆነ መልኩ ለማካሄድ በአማካሪነት ከቀጠረው ዊቬንቸር ሆልዲንግስ ከተሰኘ ሃላፊነቱ የተወሰነ ድርጅት እንዲሁም የሚዲያ አጋር ከሆነው የአፍሪካ ሬኔሳንስ ቴሌቪዥን (አርትስ ቲቪ) ጋር ዛሬ በዋናው መስሪያ ቤት ስምምነት መፈራረሙን ለኢትዮ ነጋሪ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡ የዘንድሮው ውድድር በባህር ዳር፣ ደሴ፣ መቀሌ፣አዳማ፣ድሬዳዋ፣ወላይታ፣ ሃዋሳ፣ጅማ እና አዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን በነዚህ ከተሞች በባንኩ ቅርንጫፎች የሰልጣኞች ምዝገባ ከሰኔ 18 እስከ ሰኔ 29-2016 ዓ.ም ይከናወናል፡፡ ለተመዘገቡ ሰልጣኞች በስራ ፈጠራ ዙሪያ ግንዛቤ ለማስጨበጥ የሚያስችል ስልጠና በነዚህ ከተሞች ከተሰጠ በኋላ ሰልጣኞቹ የፈጠራ መነሻ ሃሳባቸውን በፅሁፍ በባንኩ…
Read More
ካሳሁን ፎሎ የዓለም ሥራ ድርጅት አስተዳድር አባል ሆነው ተመረጡ

ካሳሁን ፎሎ የዓለም ሥራ ድርጅት አስተዳድር አባል ሆነው ተመረጡ

የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ለቀጣዮቹ 3 ዓመታት የዓለም ሥራ ድርጅት አስተዳድር አባል ሆነው ተመርጠዋል፡፡ በጀኔቫ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ባለው የዓለም ሥራ ድርጅት (ILO) 112ኛ ጉባኤ ሰኔ 3 ቀን 2016 ዓ.ም በተካሄደው ስብሰባ ለቀጣይ 3 ዓመታት በበላይነት የሚቆጣጠሩና የሚያስተዳድሩ አካላትን ከሠራተኞች ፣ከመንግሥታትና ከአሠሪዎች መካከል ለመምረጥ ባደረገው እንቅስቃሴ  ካሳሁን ፎሎ  የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ባገኙት ከፍተኛ ድምፅ የዓለም ሥራ ድርጅት የሚያስተዳድረው አካል አባል በመሆን መመረጣቸው ተገልጿል፡፡ በተመሳሳይ 112ኛ ጉባኤ ቅዳሜ ግንቦት 30 ቀን 2016 ባካሄደው ስብሰባው የዓለም ሥራ ድርጅትን በበላይነት የሚያስተዳድር (Governing Body)  ምክትል አባል ሀገራት መካከል ኢትዮጵያን አንዷ አድርጎ መርጦ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ከተወዳደሩት ሰባት ሀገራት…
Read More
በርበራ ወደብ በዓለም ባንክ የጥራት መመዘኛ ከአፍሪካ በቀዳሚነት ተመረጠ

በርበራ ወደብ በዓለም ባንክ የጥራት መመዘኛ ከአፍሪካ በቀዳሚነት ተመረጠ

የዓለም ባንክ በመላው ዓለም ያሉ ወደቦች እቃ የመጫን አቅማቸውን የተመለከተ አሁናዊ ያሉበትን ሁኔታ አስመልክቶ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ የእቃ ጫኝ ኮንቴይነር የመያዝ አቅማቸውን መሰረት በማድረግ የወደቦችን ደረጃ ያወጣው ባንኩ ኢትዮጵያ የባህር ሀይሏን ልታቋቁምበት ያሰበችበት በርበራ የተሻለ ደረጃን አግኝቷል፡፡ በባንኩ ሪፖርት መሰረት የራስ ገዟ ሶማሊላንድ ንብረት የሆነው በርበራ ወደብ ከሰሃራ በረሃ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ የመጀመሪያው ወደብ ተብሏል፡፡ በርበራ ወደብ በዓለም ካሉ ወደቦች በ103ኛ ደረጃ ላይ ሲገኝ ከሰሀራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት ደግሞ ቀዳሚው ሆኗል፡፡ ሞቃዲሾ ወደብ ከበርበራ ወደብ በመቀጠል በሁለተኝነት ሲጠቀስ የጊኒው ኮናክሪ በሶስተኝነት ሲቀመጥ  የኢኳቶሪያል ጊኒው ማለቡ ወደብ ደግሞ በአራተኝነት ተቀምጧል፡፡ ከመላው ዓለም ደግሞ የቻይናው ያንግሻህ ወደብ በአንደኝነት ሲቀመጥ…
Read More