Tigray

ራያ እና ወልቃይት አካባቢ ከትግራይ ክልል ውጪ ሆነው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድ ተወሰነ

ራያ እና ወልቃይት አካባቢ ከትግራይ ክልል ውጪ ሆነው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድ ተወሰነ

የፌዴሬሽን ምክር ቤት በአማራ እና ትግራይ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ በሚያነሱባቸው አካባቢዎች ምርጫ እንዲካሄው ውስኗል ተብሏል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ የካቲት 16፣ 2018 ባወጣው መግለጫ ከዚህ በፊት በትግራይ ክልል ስር ሆነው ምርጫ ሲካሄድባቸው የነበሩ ምርጫ ክልሎች ከክልሉ መንግስት ውጪ ሆነው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድባቸው መወሰኑን የሚገልጽ ደብዳቤ እንደደረሰው ገልጿል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብቻ ይካሄድባቸዋል ተብለው በቦርዱ መግለጫ ላይ የተጠቀሱት ምርጫ ክልሎች ሁመራ፣ አዲረመጽ፣ ኮረምኦፍላ ፣ ጠለምት እና ራያ አላማጣ ምርጫ ክልሎች እንደሆኑም ቦርዱ አስታውቋል፡፡ ቦርዱ አክሎም የክልል ምክር ቤት ምርጫ በአካባቢዎቹ ላይ የተነሳባው የይገባኛል ውዝግብ ጥያቄ በህገ መንግስት ውሳኔ መሰረት ሲፈታ እንደሚካሄድ ቦርዱ አስታውቋል።የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳድር በበኩሉ…
Read More
የፕሪቶሪያ ስምምነት አፈጻጸምን የሚከታተለው የባለሙያዎች ቡድን መቐለ ገባ

የፕሪቶሪያ ስምምነት አፈጻጸምን የሚከታተለው የባለሙያዎች ቡድን መቐለ ገባ

ለሁለት ዓመት የዘለቀውን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት እንዲቆም ምክንያት የሆነው የፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት አፈጻጸም የሚከታተል የባለሙያዎች ቡድን ትግራይ ክልል መቐለ መግባቱ ተገልጿል። ስምምነቱ እንዲፈረም ያደራደረው የአፍሪካ ህብረት የባለሙያዎችን ቡድን ያቋቋመው ከኬንያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ናይጀሪያ እና አልጀሪያ የተውጣጡ ናቸው። ይህ የባለሙያዎች ቡድን በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ታጣቂዎች ትጥቅ መፍታታቸውን፣ መሰረታዊ አገልግሎቶች መቀጠላቸውን፣ በጦርነቱ ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀድሞ ቀዬአቸው መመለሳቸውን የመከታተል ሀላፊነት ተሰጥቶታል። ዛሬ መቐለ መድረሱ የተገለጸው ይህ የባለሙያዎች ቡድን መቀመጫውን መቐለ በማድረግ የስምምነቱን አፈጻጸም ሲከታተል የቆየ ሲሆን ላለፉት ወራት በዕረፍት ላይ መቆየቱን የትግራይ ሰላምና ደህንነት ቢሮ አስታውቋል። ይህ የባለሙያዎች ቡድን ከአስተዳድራዊ ዕረፍት በኋላ ወደ መቐለ የተመለሰው በአማራ እና ትግራይ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ…
Read More
በአላማጣ እና አካባቢው በተፈጠረው አዲስ ግጭት ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ኢሰመኮ አስታወቀ

በአላማጣ እና አካባቢው በተፈጠረው አዲስ ግጭት ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ኢሰመኮ አስታወቀ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከጥር 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች አንዳንድ አዋሳኝ አካባቢዎች ከተቀሰቀሰው ግጭት ጋር በተያያዘ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን እየተከታተለ መሆኑን ገልጿል። በዚህም ይህ መግለጫ ይፋ እስከተደረገበት ጊዜ ድረስ በተለይም በጸለምት/ጠለምት፣ በመጋሌ እና አብአላ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶችን ተከትሎ የሰዎችን የሕይወት፣ የአካል ደኅንነት፣ ነጻነት እና ንብረት መብቶች ሥጋት ላይ የሚጥሉ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል ተብሏል፡፡ በተጠቀሱት አካባቢዎች የተቀሰቀሰውን ግጭት እና ወታደራዊ እንቅስቃሴ ተከትሎ ወደ ጦርነት ሊሸጋገር ይችላል የሚል ሥጋት በመፈጠሩ ሳቢያ ነዋሪዎች ‘በኮማንድ ፖስት’ ሲተዳደሩ ከቆዩት አላማጣ ከተማ እና ሌሎች አካባቢዎች የተፈናቀሉ መሆኑን እንዲሁም በሰዎች እንቅስቃሴ ላይ ገደቦች መጣላቸውን ኢሰመኮ ገልጿል፡፡ ይህ ግጭት የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነትን ተከትሎ…
Read More
በትግራይ ታጣቂዎች መካከል ያለው ውጥረት እንዳሳሰባቸው ነዋሪዎች ተናገሩ

በትግራይ ታጣቂዎች መካከል ያለው ውጥረት እንዳሳሰባቸው ነዋሪዎች ተናገሩ

በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ባለፉት ሶስት ቀናት የተፈጠሩ አለመረጋጋቶች ነዋሪዎችን እንዳስጨነቃቸው ተናግረዋል፡፡ ያነጋገርናቸው የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች እንዳሉት የትግራይ ታጣቂዎች ከነ ትጥቃቸው ወደ ከተማዋ በመግባት ሲንቀሳቀሱ የታዩ ሲሆን በተለይም የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት አካባቢ ያለው ሁኔታ አስፈሪ ነው ብለዋል፡፡ ለደህንነቱ በመስጋት ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ ነዋሪ እንዳለው ከሆነ "ከዚህ ቀደምም ብዙ አስተያየት ሰጥተናል፤ ሰሚ ግን የለም። ህዝቡ ጦርነት ሰልችቶናል ፤ እስካሁን ያደረጋችሁት የእርስ በርስ ግጭት ይበቃችኋል ብሏል። ገላጋይ ነው ያጣነው " ብለዋል። ከትናንት በስቲያ ጀምሮ የደመወዝ ይከፈለን የሚሉ ጥያቄዎችን ይዘው ወደ ከተማዋ ገብተዋል የተባሉት ታጣቂዎች ላለፉት ሁለት ቀናት የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤትን እንደከበቡ ናቸውም ተብሏል፡፡ ታጣቂዎቹ ከከልሉ ፕሬዝዳንት ጸህፈት ቤት በተጨማሪም የክልሉ መንግስት…
Read More
ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በህወሀት ምክንያት መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ተናገሩ

ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በህወሀት ምክንያት መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ተናገሩ

የሀገር መከላከያ ሰራዊት አዛዥ ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሰሜን እዝ ላይ የተፈጸመውን ጥቃት ለማሰብ በሚል በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ህወሀትን ተችተዋል። ፊልድ ማርሻል በዚህ ጊዜ እንዳሉት መከላከያ ሠራዊት ሕይወቱን ከሰጠለት ሕዝብ ውስጥ የወጡ ጥቂት ካሃዲዎች ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ከኋላው መውጋታቸው ሕመሙ ጥልቅ ነው ብለዋል። በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈፀመው ክህደት ወንድም ወንዱሙ ላይ የፈፀመው ክህደት በመሆኑ በታሪክ ልዩ እንደሚያደርገውም ጠቅሰዋል። የትግራይ ሕዝብ በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመውን ክህደት አይቀበለውም ያሉት አዛዡ  የትግራይ ሕዝብ በልጆቹ ክህደት አፍሮ፣ ተመልሰን መቐለ ስንገባ አጨብጭቦ ተቀብሎን ነበር ሲሉም አክለዋል። ስለዚህ ክህደት እና አስነዋሪ ታሪክ ስናውራ ስለ ጥቂት የሕወሓት አመራሮች እንጂ ስለ ትግራይ ሕዝብ እንዳልሆነም ገልጸዋል። የህወሀት…
Read More
የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጸብ ባንድ ጀምበር የመጣ እንዳልሆነ ጠቅላይ ሚንስትሩ ተናገሩ

የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጸብ ባንድ ጀምበር የመጣ እንዳልሆነ ጠቅላይ ሚንስትሩ ተናገሩ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ በዛሬው ዕለት ከፓርላማ አባላት ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ከኤርትራ ጋር የተፈጠረው አለመግባባት በአንድ ጀምበር የመጣ ሳይሆን ቀስ በቀስ በሂደት መምጣቱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመት በፊት የባህር ሀይሏን እንዳቋቋመች የተናገሩት ጠቅላይ ሚንስትሩ ይህ ሀይል የተቋቋመው በሀገር ውስጥ ብቻ እንዲገታ በማሰብ አልነበረም አሰብ ወደብን ከኤርትራ እንደምንረከብ በማመን ነበር ብለዋል። "ከኤርትራ መንግሥት ጋር ተስማምተን ከዚህ ወደ አሰብ የሚወስደውን መንገድ ጠግነናል ፣እንከፍታለን ብለን ጠግነናል፣ መንገዱን ከጠገንን በኋላ ግን ችግር አለብን አሰብ ወደብ ተዳክሟል አሉን። አንዳንድ ሰው ከኤርትራ ጋር የገባንበት አለመግባባት በአንድ ምሽት የመጣ ይመስለዋል እንደዛ አይደለም ታሪኩን ስለማንናገር ነው" ብለዋል ጠቅላይ ሚንስትር አብይ። ወደ አሰብ መንገድ ጠግነን ከጨረስን በኃላ '…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ14 ሚሊዮን በላይ መንገደኞች ማጓጓዙን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ14 ሚሊዮን በላይ መንገደኞች ማጓጓዙን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት 9 ወራት 14.5 ሚሊዮን መንገደኞችን ማጓጓዙን አስታውቋል፡፡ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲመሳከር የ13 በመቶ እድገት እንዳለው ዋና ስራ አስፈፃሚው መስፍን ጣሰው ተናግረዋል፡፡ አየር መንገዱ በዘጠኝ ወር ውስጥ ያገኘው ገቢ 5.6 ቢሊዮን ዶላር መሆኑንን የተናገሩት አቶ መስፍን ጣሰው ገቢውም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲተያይ የ8 በመቶ ብልጫ አሳይቷል ብለዋል፡፡ በጊዜ ማዕቀፍ 10 አዳዲስ አውሮፕላኖች የኢትዮጵያ አየር መንገድን መቀላቀላቸው የተጠቀሰ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ሶስቱ ኤርባስ A350-1000 መሆናቸው ተሰምቷል፡፡ በዘጠኝ ወሩ ውስጥ አራት አዳዲስ የበረራ መዳረሻዎችንም የኢትዮጵያ አየር መንገድ መክፈቱን ጠቅሷል፡፡ አየር መንገዱ የፊታችን እሁድ ጁን 1, 2025 ከአዲስ አበባ ወደ ተባበሩት አረብ ኢምሬት ሻርጃህ ከተማ…
Read More
በትግራይ ክልል 259 ሰዎች በፈንጅ መገደላቸው ተገለጸ

በትግራይ ክልል 259 ሰዎች በፈንጅ መገደላቸው ተገለጸ

በትግራይ ክልል ባለፈው ሁለት አመት 1664 ሰዎች በተቀበሩ ፈንጂዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገልጿል፡፡ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከተፈፀመ ወዲህ ይህንን ያህል ቁጥር ያላቸው ሰዎች ጉዳት ሲደርስባቸው ከእነዚህ ውስጥ 259ኙ ደግሞ ህይወታቸው እንዳለፈ የክልሉ መልሶ ግንባታና ልማት ድርጅት (ራዶ) አስታውቋል፡፡ አለም አቀፍ የፈንጂ ግንዛቤ ማስጨበጫ ቀንን ምክንያት በማድረግ በመቀሌ በተደረገ ስብሰባ ላይ የክልሉ መልሶ ግንባታና ልማት ድርጅት ሀላፊው አቶ ተስፋይ ገብረማሪያም እንደገለፁት የተቀበሩ ፈንጂዎችና ጥይቶች አሁንም በተለያዩ የትግራይ ክፍሎች ውስጥ ይገኛሉ፡፡ የፈንጂ አምካኝ ግብረ ሀይል አስተባባሪ የሆኑት ኮሎኔል ተስፋይ አብርሀ በበኩላቸው በክልሉ ውስጥ በየቀኑ የፈንጂ አደጋዎች እየደረሱ መሆናቸውን ገልፀው የበጀት እጥረትና ለጉዳዩ በቂ ትኩረት አለመስጠት ስራቸውን እያደናቀፈባቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ላለፉት ሁለት ዓመታት ትግራይን…
Read More
ጀነራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ሆነው ተሾሙ

ጀነራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ሆነው ተሾሙ

የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ከተመሰረተ በኃላ ላለፉት ሁለት ዓመታት የአቶ ጌታቸው ረዳ ምክትል በመሆንና የሰላምና ፀጥታ ካቢኔ ሲክሬተርያት ሀላፊ ብሎም የትግራይ ጦር አዛዥ በመሆን ሲሰሩ የቆዩት ጀነራል ታደሰ በዛሬው እለት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ሆነው ተሾመዋል። ጀነራል ታደሰ ቀደም ሲል በህወሓት አቶ ጌታቸውን በመተካት ፕሬዝዳንት እንዲሆኑ ተመርጠው ፌደራል መንግስትም ይህንኑ የህወሓት ምርጫ ተቀብሎት እንደነበር ከዚህ ቀደም ፓርቲው ማስታወቁ አይዘነጋም። ጄኔራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንትነትን የተረከቡ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጨምሮ ሚኒስትሮች፣ ተጋባዥ እንግዶች እና ሌሎች አካላት በስልጣን ርክክቡ ላይ ተገኝተዋል፡፡ ጀነራል ታደሰ ወረደ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ፣ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሠረት ተዋጊዎችን ትጥቅ ማስፈታት፣ መልሶ…
Read More
አሜሪካንን ጨምሮ ከ25 በላይ ሀገራት በትግራይ ያለው አለመረጋጋት አሳስቦናል አሉ

አሜሪካንን ጨምሮ ከ25 በላይ ሀገራት በትግራይ ያለው አለመረጋጋት አሳስቦናል አሉ

በትግራይ ክልል በጊዜያዊ አስተዳድሩ እና በእነ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ቡድን መካከል ግጭት መከሰቱን ተከትሎ የመፈንቅለ መንግስት እየተፈጸመ መሆኑን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳድር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ መናገራቸው ይታወሳል፡፡ አቶ ጌታቸው ረዳ በመቀሌ እና አዲ አበባ በሰጧቸው መግለጫዎች ላይ እንዳሉት የህወሃት አንዱ ክንፍ በጊዜያዊ አስተዳድሩ ላይ አመራሮችን መሾም፣ ማህተም መቀማት፣ ቢሮዎችን መቆጣጠር እና ሌሎች ህጋዊ ያልሆኑ ስራዎችን እያካሄደ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ይህን ተከትሎ በትግራይ ክልል አለመረጋጋት የተፈጠረ ሲሆን በክልሉ ዳግም ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚሉ ስጋቶች አይለዋል፡፡ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ከ20 በላይ ሀገራትም በትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳሳሰባቸው ባወጡት የጋራ መግለጫ ላይ ገልጸዋል፡፡ የጋራ መግለጫውን ካወጡ ሀገራት መካከል አሜሪካ፣ ብሪታንያ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ጀርመን፣ፈረንሳይ፣ ስዊድን፣ ቤልጂየም እና…
Read More