29
Aug
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ በሶማሊያ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ አሳሳቢ ነው ብሏል። ሚኒስቴሩ መግለጫውን ያወጣው ግብጽ ከሶስት አስርት አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሶማሊያ የጦር መሳሪያ መላኳ ከተነገረ በኋላ ነው። ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር በተፈራረመችው የመግባቢያ ስምምነት ምክንያት ከሶማሊያ ጋር ግንኙነቷ ሲሻክር፥ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጋር ቅራኔ ውስጥ ያለችው ግብጽ ለሶማሊያ ድጋፏን አሳይታለች። ግብጽ በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ከሞቃዲሾ ጋር የወታደራዊ ደህንነት ስምምነት የተፈራረመች ሲሆን በሶማሊያ ለሚሰማራው አዲስ የሰላም አስከባሪ ተልእኮ ወታደሮች ለመላክ ፈቃደኝነቷን መግለጿም ይታወሳል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው ግብጽን በስም ባይጠቅስም በሶማሊያ የተሰማራው የአፍሪካ ህብረት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (አትሚስ) ሽግግር ሂደት ሳይጠናቀቅ በሞቃዲሾ አዲስ የሰላም አስከባሪ ተልዕኮ…