Eritrea

የኤርትራ ጦር ከአማጺ ጋር በመተባበር ወደ ኢትዮጵያ ግዛት መግባቱ ተገለጸ

የኤርትራ ጦር ከአማጺ ጋር በመተባበር ወደ ኢትዮጵያ ግዛት መግባቱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር እንዳስታወቀው ኤርትራ ባለፉት ቀናት አዲስ ወታደሮችን ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን አስታውቋልል። ሚንስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ለኤርትራ አቻቸው ኦስማን ሳሌህ በጻፉት ደብዳቤ የኤርትራ ጦር ከአማጺያን ጋር በመተባበር በሰሜን ምስራቅ በኩል ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን አስታውቋል። ወደ ኢትዮጵያ የገቡት የኤርትራ ወታደሮችም ከአማጺያን ጋር በመቀናጀት ወታደራዊ እንቅስቃሴ እያደረጉ እንደሆኑም ተገልጿል። በመሆኑም እነዚህ የኤርትራ ወታደሮች ከኢትዮጵያ ባስቸኳይ እንዲወጡም ጠይቋል። የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ በደብዳቤው ላይ ከኤርትራ ጋር የገቡበትን አለመግባባት በዲፕሎማሲ ለመፍታት ዝግጁ እንደሆነም ገልጿል። ሚንስትሩ አክለውም በተለይ ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት እና የአሰብ ወደብን ለማግኘት ያቀረበቻቸውን ጥያቄዎች ጨምሮ ሌሎች ፍላጎቶችን ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ ለመወያየት ዝግጁ እንደሆነችም ተጠቅሷል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ባሳለፍነው…
Read More
ኤርትራ ከኢጋድ ለመልቀቅ ያሳለፈችውን ውሳኔ ዳግም እንድታጤነው ተጠየቀች

ኤርትራ ከኢጋድ ለመልቀቅ ያሳለፈችውን ውሳኔ ዳግም እንድታጤነው ተጠየቀች

የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ፤ የኤርትራ መንግሥት ከድርጅቱ የመውጣት ውሳኔ ያሳለፈው “ተጨባጭ ሃሳቦች ወይም በአይነተኛ ተቋማዊ ወይም የፖሊሲ ማሻሻያዎች ዙሪያ ተሳትፎ” ሳያቀርብ መሆኑን በማንሳት ቅሬታውን ገልጿል። ኢጋድ ይህንን ውሳኔ በይፋዊ የቃል ማስታወሻ መግባቱን አረጋግጧል። ሆኖም ግን፣ ሴክሬታሪያቱ ለድርጅቱ የተላከው ማስታወሻ ከማንኛውም ቀደም ያለ ውይይት ውጪ መሆኑን ጠቁሟል። ኤርትራ ለሁለት አሥርት ዓመታት ያህል በራሷ ፍላጎት አባልነቷን ካገደች በኋላ፣ እ.ኤ.አ. ሰኔ 2023 በተካሄደው 14ኛው የልዩ መሪዎች ጉባኤ ላይ በሁሉም አባል አገሮች በሞቃት አቀባበል ወደ ድርጅቱ ተመልሳ ነበር ብሏል። በዚያን ወቅት፣ መመለሷ “ሁሉን አቀፍነት፣ የክልላዊ ወንድማማችነት እና የታደሰ ትብብር የጋራ ቁርጠኝነት” ማሳያ እንደነበር ድርጅቱ አስታውሷል። ነገር ግን፣ ኢጋድ ከሰኔ 2023…
Read More
ኢትዮጵያ የኤርትራ ፖሊሲዬ “ሙሉ በሙሉ ከሸፈ” አለች

ኢትዮጵያ የኤርትራ ፖሊሲዬ “ሙሉ በሙሉ ከሸፈ” አለች

ከኤርትራ ጋር በትብብር ላይ የተመሰረተ፣ አዎንታዊ እና ገንቢ የረጅም ጊዜ ግንኙነትን ለመመስረት የሚያስችል አካሄድን ወይም ፖሊሲን ስንከተል ነበር ያሉት የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ፖሊሲው አሁን "ሙሉ በሙሉ ከሽፏል" ብለዋል። ለፖሊሲው መክሸፍ "አጋጣሚውን መጠቀም አልተቻለም" ያሉትን የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን የኤርትራ አገዛዝ ተጠያቂ አድርገዋል። አገዛዙ በኢትዮጵያ ላይ እየተከተለ ባለው 'የተሳሳተ' ፖሊሲ ምክንያት ዘላቂ ግንኙነት ለመመስረት የተደረጉ ሙከራዎች ሁሉ ሙሉ በሙሉ መክሸፋቸውንም ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ትኩረቱን በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲና በአፍሪካ ቀንድ ዙሪያ ባሉ ወቅታዊ የፖለቲካና የደህንነት ሁነቶች ላይአድርጎ ትናንት ሐሙስ ህዳር 4 ቀን 2018 ዓ/ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ መኮንን አዳራሽ በተካሄደ የውይይት መድረክ ላይ የተናገሩት። በመድረኩ ሁነቶችን…
Read More
ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በህወሀት ምክንያት መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ተናገሩ

ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በህወሀት ምክንያት መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ተናገሩ

የሀገር መከላከያ ሰራዊት አዛዥ ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሰሜን እዝ ላይ የተፈጸመውን ጥቃት ለማሰብ በሚል በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ህወሀትን ተችተዋል። ፊልድ ማርሻል በዚህ ጊዜ እንዳሉት መከላከያ ሠራዊት ሕይወቱን ከሰጠለት ሕዝብ ውስጥ የወጡ ጥቂት ካሃዲዎች ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ከኋላው መውጋታቸው ሕመሙ ጥልቅ ነው ብለዋል። በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈፀመው ክህደት ወንድም ወንዱሙ ላይ የፈፀመው ክህደት በመሆኑ በታሪክ ልዩ እንደሚያደርገውም ጠቅሰዋል። የትግራይ ሕዝብ በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመውን ክህደት አይቀበለውም ያሉት አዛዡ  የትግራይ ሕዝብ በልጆቹ ክህደት አፍሮ፣ ተመልሰን መቐለ ስንገባ አጨብጭቦ ተቀብሎን ነበር ሲሉም አክለዋል። ስለዚህ ክህደት እና አስነዋሪ ታሪክ ስናውራ ስለ ጥቂት የሕወሓት አመራሮች እንጂ ስለ ትግራይ ሕዝብ እንዳልሆነም ገልጸዋል። የህወሀት…
Read More
የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጸብ ባንድ ጀምበር የመጣ እንዳልሆነ ጠቅላይ ሚንስትሩ ተናገሩ

የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጸብ ባንድ ጀምበር የመጣ እንዳልሆነ ጠቅላይ ሚንስትሩ ተናገሩ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ በዛሬው ዕለት ከፓርላማ አባላት ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ከኤርትራ ጋር የተፈጠረው አለመግባባት በአንድ ጀምበር የመጣ ሳይሆን ቀስ በቀስ በሂደት መምጣቱን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ከስድስት ዓመት በፊት የባህር ሀይሏን እንዳቋቋመች የተናገሩት ጠቅላይ ሚንስትሩ ይህ ሀይል የተቋቋመው በሀገር ውስጥ ብቻ እንዲገታ በማሰብ አልነበረም አሰብ ወደብን ከኤርትራ እንደምንረከብ በማመን ነበር ብለዋል። "ከኤርትራ መንግሥት ጋር ተስማምተን ከዚህ ወደ አሰብ የሚወስደውን መንገድ ጠግነናል ፣እንከፍታለን ብለን ጠግነናል፣ መንገዱን ከጠገንን በኋላ ግን ችግር አለብን አሰብ ወደብ ተዳክሟል አሉን። አንዳንድ ሰው ከኤርትራ ጋር የገባንበት አለመግባባት በአንድ ምሽት የመጣ ይመስለዋል እንደዛ አይደለም ታሪኩን ስለማንናገር ነው" ብለዋል ጠቅላይ ሚንስትር አብይ። ወደ አሰብ መንገድ ጠግነን ከጨረስን በኃላ '…
Read More
ኢትዮጵያ የአሰብ ወደብን ከኤርትራ መረከቧ አይቀሬ መሆኑን ገለጸች

ኢትዮጵያ የአሰብ ወደብን ከኤርትራ መረከቧ አይቀሬ መሆኑን ገለጸች

የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ምክትል አዛዥ ኮሞዶር ተገኝ ለታ እንዳሉት የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ መመለስ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ሰላምና መረጋጋት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። ምክትል አዛዡ ይህን የተናገሩት ጥቅምት 8 ቀን 2018 ዓ.ም በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት፣ በመከላከያ ዋር ኮሌጅና በሠመራ ዩኒቨርሲቲ ትብብር “የሁለቱ የውሃ ሥርዓቶችና የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ነፃነት፣ የዓባይና የቀይ ባሕር ትስስር እና የአፋር ክልልን ስትራቴጂካዊ ሚና መዳሰስ” በሚል ርዕስ በሠመራ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደ የምክክር መድረክ ላይ ነው። በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ምክትል አዛዥ ኮሞዶር ተገኝ ለታ የኢትዮጵያ ወደብ አልባ መሆን በሀገሪቱ ላይ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ቀንድ ሊኖረው የሚችለው ኢኮኖሚዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊ መዘዝን መረዳት ተገቢ መሆኑንም አጽኖት ሰጥተው…
Read More
አሜሪካ ኤርትራን ጨምሮ በ10 ሀገራት ያሏትን ኢምባሲዎች ልዘጋ ነው

አሜሪካ ኤርትራን ጨምሮ በ10 ሀገራት ያሏትን ኢምባሲዎች ልዘጋ ነው

የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳድር መንግስት ወጪ ቅነሳ ላይ ሲሆን አሁን ደግሞ ኢምባሲዎችን ለመዝጋት ማሰባቸው ተገልጿል፡፡ ፖለቲኮ እንደዘገበው ከሆነ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የወጪ ቅነሳ አዲስ እቅድ አውጥቷል፡፡ በዚህ እቅድ መሰረትም የመስሪያ ቤቱን አመታዊ ወጪ በግማሽ በመቶ ለመቀነስ መታሰቡ ተገልጿል፡፡ እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ ከቀረቡ  ምክረ ሀሳቦች መካከል በዓለም ላይ ያሉ የአሜሪካ ኢምባሲዎች እና ቆንሱላ ጽህፈት ቤቶችን ለመዝጋት ታቅዷል ተብሏል፡፡ በዓለማችን ቁጥር አንድ ባለጸጋ ኢለን መስክ ምክር የሚመራው የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳድር መንግስት አሁን ደግሞ ትኩረቱን ወደ ኢምባሲዎች መዝጋት አዙሯል፡፡ ከቀረቡት ምክረ ሀሳቦች ውስጥ 10 የአሜሪካ ኤምባሲዎች እና 17 ቆንስላ ጽህፈት ቤቶችን ለመዝጋት መታቀዱ ተገልጿል፡፡ በእቅድ ደረጃ እንዲዘጉ ከተባሉት ኤምባሲዎች እና…
Read More
ኤርትራዊያንን በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መኪና ሲያጓጉዙ የተገኙ ወታደሮች በእስራት ተቀጡ

ኤርትራዊያንን በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መኪና ሲያጓጉዙ የተገኙ ወታደሮች በእስራት ተቀጡ

በሰዎች ዝውውር የተከሰሱ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በእሥራት ተቀጥተዋል። በህገ ወጥ የሠዎች ዝውውር ተሠማርተዋል የተባሉ አንድ ከፍተኛ የአገር መከላከያ ሠራዊት አዛዥን ጨምሮ ሁለት የሠራዊቱ አባላት በ8 ዓመት ከ5 ወር ፅኑ እስራት ተቀጥተዋል፡፡ አባላቱ ቅጣቱ የተላለፈባቸው ትናንት በአርባምንጭ ከተማ በተሰየመው የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባሳለፈው የፍርድ ውሳኔ ነው  ተብሏል፡፡ ቅጣቱ የተወሰነው በሠራዊቱ የደቡብ ዕዝ 202ኛ ኮር 1ኛ ሬጅመንት አዛዥ ሻምበል መብራቱ ታዴ እና በሬጅመንቱ የኦራል አሽከርካሪ በሆነው ወታደር ጌታቸው ክብረት በተባሉት  ላይ እንደሆነ ዶቸቪሌ ዘግቧል። አዛዡ እና የሰራዊቱ አባል ቅጣቱ የተወሰነባቸው ህዳር 16 2016 ዓ.ም 52 ኤርትራዊያንን በሠራዊቱ የኦራል ተሽከርካሪ በመጫን ወደ ኬኒያ በማሻገር ላይ እንዳሉ በመያዛቸው መሆኑን የጋሞ ዞን ከፍተኛ…
Read More
የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ በኤርትራ ጉዳይ የሰጡት ሀሳብ የግላቸው እንጂ የመንግስት አቋም አይደለም ተባለ

የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ በኤርትራ ጉዳይ የሰጡት ሀሳብ የግላቸው እንጂ የመንግስት አቋም አይደለም ተባለ

የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ በኤርትራ ጉዳይ የሰጡት ሀሳብ የመንግስት አቋም አለመሆኑን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ በመግለጫው ላይ ከጋዜጠኞች ከቀረበላቸው ጥያቄዎች መካከል የቀድሞው የኢትዮጵያ አምባሳደር ተሾመ ሙላቱ (ዶ/ር) ኤርትራን አስመልክቶ ያጋሩት ጽሁፍ ነው። የቀድሞው ፕሬዝዳንት ከሁለት ሳምንትት በፊት አልጀዚራ ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ "የኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት ለመቀስቀስ እየተንቀሳቀሰ ነው፤ በምስራቅ አፍሪካ አዲስ ግጭት እንዳይከፈት ለማስቆም ጊዜው አሁን ነው" ማለታቸው ይታወሳል። የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል በኤክስ ገጻቸው ባጋሩት ጽሁፍ በቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት የተነሱትን ነጥቦች አጣጥለዋል። ስለ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ጽሁፍ ኤርትራ ምላሽ የተጠየቁት አምባሳደር…
Read More
ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ለነበራት ወዳጅነት መበላሸት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን ተጠያቂ አደረገች

ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ለነበራት ወዳጅነት መበላሸት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን ተጠያቂ አደረገች

ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር የነበራት ግንኙነት የተበላሸው በጠቅላይ ሚኒስር አብይ አህመድ አማካኝነት ነው ብላለች፡፡ በኤርትራ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት እንደ ቀድሞው አለመሆኑን በደቡብ ሱዳን የኤርትራ አምባሳደር የሆኑት ዮሃንስ ተክለሚካኤል ተናግረዋል። አምባሳደሩ ይህንን የተናገሩት ባልተለመደ ሁኔታ በብሪታኒያ የኤርትራ ኤምባሲ የዩቲዩብ ቻናል ላይ በሰጡት ቃለ ምልልስ ሲሆን፤ ቪዲዮው ይፋ ከተደረገ ከሰዓታት በኋላ እንዲነሳ መደረጉን ቢቢሲ ዘግቧል። ተሻሽሎ የነበረው የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት፤ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በህወሓት መካከል የፕሪቶሪያ ስምምነት ከተፈረመ በኋላ በይፋ የተባለ ነገር ባይኖርም የአገራቱ ግንኙነት ተቀዛቅዟል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ እና የስልክ ግንኙነት መቋረጥ ግንኙነቱ ስለመሻከሩ ማሳያ መሆኑ በተደጋጋሚ ሲጠቀስ ቆይቷል። በደቡብ ሱዳን የኤርትራ አምባሳደር ዮሃንስ ተክለሚካኤል ‘ኤርትራ ኤምባሲ ሚዲያ’ (Eritrea…
Read More