06
Mar
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በእስራኤል-ኢራን ጦርነት ምክንያት በሳምንት የ137 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እያስተናገደ መሆኑን ገለጸ ከሰባት ቀናት በፊት የተጀመረው የእስራኤል-ኢራን ጦርነት ጉዳቱ በመላው ዓለም ላይ ሲሆን ኢትዮጵያም የጦርነቱ ተጎጂ ሆኗ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንዳስታወቀው በዚህ ጦርነት ምክንያት በየሳምንቱ ወደ መካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የካርጎ በረራን ሳይጨምር የመንገደኞችን ብቻ 101 በላይ በረራዎችን እየሰረዘ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በረራዎቹ በመሰረዛቸው ምክንያትም እስከ 137 ሚሊዮን ዶላር በማጣት ላይ መሆኑን አስታውቋል፡፡ አየር መንገዱ የእስራኤል- ኢራን ጦርነት ከመጀመሩ በፊት በቀን ወደ ዱባይ ሦስት ጊዜ ፣ ወደ ሻርጃ አንድ ጊዜ፣ ወደ እስራኤል ሦስት ጊዜ፣ ወደ አቡዳቢ፣ ወደ አማን ሁለቴ መንገደኞችን ያመላልስ ነበር። በጦርነቱ ምክንያት አየር መንገዱ በአማካኝ በየዕለቱ 15…