መነሻ ገፅ

የክልል አየር ማረፊያዎች ዓለም አቀፍ በረራዎች ማስተናገድ ሊጀምሩ ነው

የክልል አየር ማረፊያዎች ዓለም አቀፍ በረራዎች ማስተናገድ ሊጀምሩ ነው

ዓለም አቀፍ በረራዎችን ከአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በተጨማሪ በሌሎች የክልል አየር ማረፊያዎች ማስተናገድ ሊጀመር መሆኑን የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታውቋል። ባለስልጣኑ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዶ/ር አለሙ ስሜ፣ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሃንስ አበራ፣ ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች እና የግል አየር ትራንስፖርት ኦፕሬተር ተወካዮች በተገኙበት፤ የአየር ትራንስፖርት ዘርፍ የባለድሻ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ አካሂዷል። በባለስልጣኑ የአየር ትራንስፖርትና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች አማካሪ አቶ እንደሻው ይገዙ ባቀረቡት ሪፖርት፤ በ2018 ዓ.ም ዓለም አቀፍ በረራዎችን ከአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በተጨማሪ በሌሎች የሀገሪቱ ክልል ኤርፖርቶች ማስተናገድ እንደሚጀመር ተናግረዋል። "የክልል ኤርፖርቶችን ማስተሳሰር የቱሪዝም ፍሰቱ እንዲጨምር እንዲሁም የደንበኛውን እንግልት መቀነስ የሚያስችል ነው" ያሉት አቶ…
Read More
ጃፓን ለአትሌት አበበ ቢቂላ የመታሰቢያ መንገድ ሰየመች

ጃፓን ለአትሌት አበበ ቢቂላ የመታሰቢያ መንገድ ሰየመች

በጃፓን ካሳማ ከተማ ለአትሌት አበበ ቢቂላ የመታሰቢያ መንገድ ተሰየመ በጃፓን ካሳማ ከተማ አትሌት አበበ ቢቂላን ለማስታወስ የግማሽ ማራቶን መንገድ በስሙ መሰየሙን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የስያሜ ስነ-ስርዓቱ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበልን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራን፣ በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር ዳባ ደበሌን እና የካሳማ ከተማ ከንቲባን ጨምሮ በርካታ ባለስልጣናት በተገኙበት ተከናውኗል። በስነ-ስርዓቱ ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ይህ የመታሰቢያ ስያሜ ለአትሌቱ ክብር ከመስጠት በተጨማሪ በኢትዮጵያ እና በጃፓን መካከል ያለውን ጥብቅ ወዳጅነት እና የባህል ትስስር የሚያሳይ እንደሆነ ገልጸዋል። አትሌት አበበ ቢቂላ በ1964ቱ የቶኪዮ ኦሎምፒክ ያገኘው ድል ኢትዮጵያን ያስጠራ ብቻ ሳይሆን በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነትም አጠናክሯል ብለዋል። በጃፓን…
Read More
ልማት ባንክ ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር መሰብሰቡን አስታወቀ

ልማት ባንክ ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር መሰብሰቡን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ወቅት፣ ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ የብድር ክምችት ማሰባሰቡን ይፋ አድርጓል። ይህ ባንኩ ለተለያዩ ፕሮጀክቶች አበድሮ የነበረውን ገንዘብ ከባለዕዳዎች መልሶ የሰበሰበው መጠን አፈጻጸም ከታለመለት ግብ በ5 በመቶ ብልጫ ያለው ሲሆን፣ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ደግሞ የ51.6 በመቶ ዕድገት ማሳየቱ ተገልጿል። የባንኩ ዋና ትኩረት ለኢንዱስትሪ፣ ለግብርና እና ለሌሎች ቁልፍ የኢኮኖሚ ዘርፎች የፋይናንስ ድጋፍ ማድረግ እንደሆነ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በዚሁ በጀት ዓመት 18.0 ቢሊዮን ብር ገቢ በማሰባሰብ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ30.7 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ተጠቅሷል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በግብርና፣ ማዕድን ማውጣት፣ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለሚሰማሩ ኢንቨስትመንቶች የገንዘብ አቅርቦት የሚያመቻች መንግስታዊ ተቋም…
Read More
በኢትዮጵያ ከተመዘገቡ 6 ሺህ ቤት አልሚዎች ውስጥ ስራ ላይ ያሉት ከ400 አይበልጥም ተባለ

በኢትዮጵያ ከተመዘገቡ 6 ሺህ ቤት አልሚዎች ውስጥ ስራ ላይ ያሉት ከ400 አይበልጥም ተባለ

ከፌዴራልና ከክልል በአጠቃላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሪል እስቴት ልማት ዘርፍ ለመሳተፍ ፈቃድ የወሰዱና የተመዘገቡ 6 ሺሕ የሚሆኑ አልሚዎች ያሉ ቢሆኑም፤ በሥራ ላይ የሚገኙት ግን ከ400 እንደማይበልጡ የኢትዮጵያ ሪል እስቴት አልሚዎች ማህበር አስታውቋል። የሪል እስቴት ዘርፉ ከአልሚዎች፣ ከገዢዎችና ከፋይናንስ ተቋማት ጨምሮ፤ በርካታ ችግሮች እና ተነሳሽነት ያልነበረበት እንደነበር የገለጹት፤ የማህበሩ ም/ፕሬዝዳንት ኢንጂነር ጀበል ጀማል ናቸው። ያለውን ችግር ለማስተካከልና በዘርፉ መተጋገዝ ካለና በጋራ መስራት ከተቻለ፤ የተሻለ ለውጥ ሊመጣ እንደሚችል በማመን የሪል እስቴት አልሚዎች ማሕበር መመስረት መቻሉንም አንስተዋል። ማሕበሩ ከመንግሥትና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በ29 አባላት መመስረት እንደቻለ አስታውሰው፤ አሁን ላይ ከ100 በላይ አባልትን በውስጡ መያዙን ገልጸዋል። አሁን ላይ እንደሀገር ከተመዘገቡት 6 ሺሕ…
Read More
ኢትዮጵያ በውጭ ሀገራት የሚሰማሩ ስራ ተቋራጭ ድርጅቶችን የማሳደግ እቅድ እንዳላት ተገለጸ

ኢትዮጵያ በውጭ ሀገራት የሚሰማሩ ስራ ተቋራጭ ድርጅቶችን የማሳደግ እቅድ እንዳላት ተገለጸ

10 የስራ ተቋራጭ ድርጅቶች ከኢትዮጵያ ውጪ ውጪ ባሉ ሀገራት መሰማራታቸውን የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚንስቴር አስታውቋል ሚንስቴሩ በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የተሰማሩ የኢትዮጵያ ስራ ተቋራጭ ድርጅቶችን ቁጥር 20 የማድረስ እቅድ መያዙን ገልጿል። የሀገራቱን አስፈላጊ መስፈርት አሟልተውና በጨረታ አሸንፈው በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ በኮንስትራክሽን ሥራዎች ላይ የሚሳተፉ ተቋራጮችን ቁጥር ወደ 20 ከፍ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር አስታውቋል። የሚንስትሩ ሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኢትዮጵያ በዴቻ፤ "ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የግንባታ ሥራ ለማከናወን ፈቃድ ተሰጥቷቸው በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የኮንትራት ሥራዎችን ወስደው በግንባታ ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የግንባታ ስራ ተቋራጮች ቁጥር ከ10 አይበልጥም" ብለዋል፡፡ በመሆኑም ሚኒስቴሩ ይህን የግንባታ ሥራ ተቋራጮች…
Read More
የኬንያው ኪሲቢ ባንክ የኢትዮጵያን ባንክ 40 በመቶ ድርሻ ለመግዛት ንግግር ጀመረ

የኬንያው ኪሲቢ ባንክ የኢትዮጵያን ባንክ 40 በመቶ ድርሻ ለመግዛት ንግግር ጀመረ

ብሔራዊ ባንክ ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው እንዲሰሩ የሚፈቅድ ህግ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ይህንን ተከትሎም የኬንያው  ኬሲቢ ግሩፕ በኢትዮጵያ ባንክ ኢንቨስትመንት ለመስራት በንግግር ላይ መሆኑን ቢዝነስ ዴይሊ ዘግቧል፡፡ ባንኩ በሚቀጥሉት 18 ወራት ውስጥ በኢትዮጵያ የሚገኝን አንድ ባንክ 40 ከመቶ ድርሻን ለመግዛት ንግግር በማድረግ ላይ እንደሆነ ተገልጿል። ይሁንና ኬሲቢ ከየትኛው የኢትዮጵያ ባንክ ጋር ንግግር እንደጀመረ በዘገባው ላይ አልተገለፀም። ያም ሆነ ይህ የኬንያ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ሰፊ የባንክ ስራዎችን በመስራት በኢትዮጵያ ተመራጭ ባንክ ለመሆን እቅድ ይዟል። ብሔራዊ ባንክ ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣዉ መግለጫ መመሪያው የውጭ ተዋናዮች የባንክ ዘርፉን እንዲቀላቀሉባቸው በርካታ መንገዶችን ያቀርባል፤ ከእነዚህም መካከል ቅርንጫፍ…
Read More
የጉምሩክ ቀረጥ ገቢ ባለፉት 7 ዓመታት በግማሽ መቀነሱ ተነገረ

የጉምሩክ ቀረጥ ገቢ ባለፉት 7 ዓመታት በግማሽ መቀነሱ ተነገረ

ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ የጉምሩክ ቀረጥና ተጨማሪ ቀረጥ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት አንጻር በግማሽ መቀነሱ ተገለጸ። ይህ ቅናሽ በዋናነት ከውጭ የሚገቡ የሸቀጦች መጠን እና ዋጋ በመቀነሱ ምክንያት እንደሆነ ተጠቁሟል። እኤአ 2015/16 ጀምሮ የነበረው የጉምሩክ ቀረጥና ተጨማሪ ቀረጥ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 2.1% የነበረ ሲሆን፣ ይህ አሃዝ በ2022/23 ወደ 1.0% ዝቅ ብሏል። የዚህ መቀነስ ዋነኛ ምክንያት፣ ከውጭ የሚገቡ የሸቀጦች መጠን ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ከ24% ወደ 10% በመውረዱ እንደሆነ የገንዘብ ሚኒስቴር የሰሞኑን ጥናት ያመለክታል። ይህ የገቢ ቅናሽ አጠቃላይ የግብር እና የሀገር ውስጥ ምርት ጥምርታ መውረድ ውስጥ አንድ አራተኛውን ይዟል። ከ2015/16 እስከ 2021/22 ባለው ጊዜ ውስጥ፣ የውጭ ምርቶች መጠን መቀነስ በዋነኝነት በካፒታል…
Read More
ቻይና ሰራሹ ሲኖ ትራክ ተሽከርካሪ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ ተከለከለ

ቻይና ሰራሹ ሲኖ ትራክ ተሽከርካሪ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ ተከለከለ

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከሲኖትራክ ምርት ተሽከርካሪዎች ጋር ተያይዞ በታየው የጥራትና ቴክኒክ ጉድለት ምክንያት፣ እነዚህ ተሽከርካሪዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገቡ እገዳ መጣሉን አሳውቋል። ይህ ውሳኔ በሰዎች ህይወት ላይ በተደጋጋሚ አደጋ እየደረሰ በመሆኑ እንደተወሰነ ኢትዮ ነጋሪ ለጉምሩክ ኮሚሽን በተጻፈ ከሰርኩላር ደብዳቤ ላይ ተመልክቷል። ሚኒስቴሩ በጉምሩክ ኮሚሽን በኩል ለጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች በሙሉ ባስተላለፈው መረጃ መሰረት፣ የሲኖትራክ ካምፓኒው የጥራት ጉድለቶቹን እስኪያስተካክል ድረስ ከግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ምንም ዓይነት የሲኖትራክ ተሽከርካሪ ማስገቢያ ፍቃድ እንደማይሰጥ አስታውቋል። ከዚህም ባሻገር፣ ሚኒስቴሩ ፊርማና ማህተም በማስመሰል የሲኖትራክ ማስገቢያ ፍቃድ በማዘጋጀት ተሽከርካሪዎችን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት የሚሞክሩ ሰዎች መኖራቸውን መረጃ እንዳገኘ ገልጿል። ይህን ተከትሎ፣ ከግንቦት 27 ቀን 2017…
Read More
ከአዲስ አበባ-ሀርጌሳ- ጅቡቲ የአውቶቡስ ትራንስፖርት ሊጀመር ነው

ከአዲስ አበባ-ሀርጌሳ- ጅቡቲ የአውቶቡስ ትራንስፖርት ሊጀመር ነው

ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ ወራት ወደ ሶማሊላንድ እና ጅቡቲ የአውቶቡስ ትራንስፖርት አገልግሎት የማስጀመር እቅድ እንዳላት ገልጻለች። የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ባረኦ ሀሰን መቀመጫውን ኬኒያ ናይሮቢ ያደረገው አቢሲኒያ ሌግዠሪ ኮች ባለቤት እና ማኔጅመንት አባላት ጋር ተወያይተዋል። አቶ በሪኦ በዚህ ጊዜ እንዳሉት የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚንስቴር በተያዘው በጀት አመት ኬኒያ፣ ጅቡቲ እና ሶማሌላንድ በየብስ ትራንስፖርት ለማገናኘት እቅድ መያዙን ገልጸዋል። አገልግሎቱን የመንግስትና ግሉን ዘርፍ ትብብር በማጠናከር በጋራ እንደሚሰራም ሚንስቴር ዴዔታው ተናግረዋል። በመሆኑም እንደሚኒስቴር መስሪያቤት በሁለቱ ሀገራት በትብብር ለመስራት አስፈላጊ የሆኑ የህግ ማዕቀፎችን የማመቻቸቱን ስራ በትኩረት እንደሚሰራ እና በድርጅቱ በኩል አስፈላጊውን ሂደት አሟልተው እንዲመጡ ከስምምነት መደረሱን ሚንስቴሩ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ ያወጣው መግለጫ ያስረዳል። የአቢሲኒያ ሌግዠሪ…
Read More
የኢትዮጵያ ሙቀት በየዓመቱ ከአንድ ድግሪ ሴልሺየስ በላይ እየጨመረ መሆኑ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሙቀት በየዓመቱ ከአንድ ድግሪ ሴልሺየስ በላይ እየጨመረ መሆኑ ተገለጸ

በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በኢትዮጵያ የሙቀት መጠን በየዓመቱ በአማካይ ከ1 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ እየጨመረ ነው ተብሏል ኢትዮጵያ ለአለም ሀገራት የሙቀት መጨመር ያላት የበካይ ጋዝ ልቀት ድርሻ ግን 0.04 በመቶ ነው ተብሏል፡፡ ያደጉት ሀገራት ለአፍሪካ በየጉባኤው ቃል የሚገቡትን የአየር ንብረት ለውጥ መደገፊያ የፋይናንስ ድጋፍ እየሰጡ ስላልሆነ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የሚሰራው ስራ የሚፈለገውን ያህል መሆን አልቻለም ተብሏል፡፡ ይህ የተነገረው በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የሚመክረውና ኢትዮጵያ ከጳጉሜ 3 እስከ 5 ከምታሰናዳው ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ አስቀድሞ በተሰናዳ ዝግጅት ላይ ነው፡፡ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዛሬ ያሰናዳውና ነገም የሚቀጥለው ጉባኤና ኢግዚብሽን ከዋናው ጉባኤ በፊት የሚደረግ ቅድመ ጉባኤ ስለመሆኑ ተናግሯል፡፡ በዝግጅቱ መክፈቻ…
Read More