TPLF

ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ውስጥ ተሰረዘ

ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ውስጥ ተሰረዘ

ሕወሀት በሽብርተኝነት ከተፈረጀ ከ22 ወራት በኋላ ውሳኔው ተሽሯል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከሽብርተኛ ድርጅት እንዲሠረዝ በአብላጫ ድምጽ ወስኗል። ምክር ቤቱ ዛሬ ባሄደው ልዩ ስብሰባ ህወሓትን ከሽብርተኛ መዝገብ ለማንሳት በቀረበለት የውሳኔ ሀሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል። ለሰሜኑ ጦርነት ሰላማዊ መፍትሄ ለመስጠት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በኢትዮጵያ መንግስትና በህወሓት መካከል የሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል። በተፈረመው የሰላም ስምምነት መሰረትም በፌደራል መንግስት እና በህወሓት በኩል ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል። ስምምነቱ የፌደራል መንግስት በትግራይ ክልል መሰረታዊ አገልግሎቶች እንዲጀመሩ እና የሰብዓዊ እርዳታ ለተጎጂዎች እንዲቀርብ አድርጓል። ህወሓትም ታጣቂዎቹን ወደ ካምፕ በመሰብሰብ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን…
Read More
ኢትዮጵያ የአሜሪካ ሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርትን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ የአሜሪካ ሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርትን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ጥሰትን በሚመለከት በአሜሪካ የወጣውን መግለጫ ውድቅ አደረገችየአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ሁሉም ተሳታፊዎች የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸማቸውን አስታውቋል። ዋሽንግተን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተከስቷል ሲል የደረሰችበትን ድምዳሜ የኢትዮጵያ መንግሥት በፍፁም እንደማይቀበለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ጉዳዩን በተመለከተ ያወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን እና የተመድ የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር በጋራ ካደረጉት ምርመራ አንፃር ሲታይ ምንም አዲስ ግኝት ያልተካተተበት ነው ብሏል።  በመሆኑም የኢትዮጵያ መንግሥት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ያቀረበበትን ባዶ ውግዘት በፍፁም እንደማይቀበለው ገልጿል።  የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ያወጣው መግለጫ አንድን ወገን ብቻ…
Read More
ኢትዮጵያ ከጦርነት ውድመት ለማገገም 20 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ተባለ

ኢትዮጵያ ከጦርነት ውድመት ለማገገም 20 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ተባለ

ኢትዮጵያ በጦርነት ከደረሰባት ውድመት ለማገገም 20 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ተባለ በኢትዮጵያ ከሁለት ዓመት በፊት ህወሀት በሀገር መከላከያ የሰሜን እዝ ላይ ጥቃት ማድረሱን ተከትሎ ነበር ጦርነት የተነሳው። በዚህ ጦርነት ምክንያት 800 000 ዜጎች ህይወታቸው እንዳለፈ ሲገለጽ የግለሰቦች እና የመንግስት መሰረተ ልማቶች ወድመዋል። ጦርነቱ አሁን ላይ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የሰላም ስምምነት ተፈርሞ ጦርነቱ ቆሟል። ይህ ለሁለት ዓመት የዘለቀው ጦርነት የወደሙ መሰረተ ልማቶችን እና ሌሎች ሀብቶችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ 20 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የፋይናንስ ሚንስቴር ገልጿል። ጦርነቱ ክፉኛ የጎዳቸው ትግራይ ፣አማራ እና አፋር ክልሎች በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ከደረሰባቸው ጉዳት እንዲያገግሙ 20 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋልም ተብሏል። ይህ የመልሶ ግንባታ በጀት ከፌደራል መንግሥት ፣ ዓለም…
Read More
ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

ከሰሞኑ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር በአዲስ አበባ የነበሩት ጌታቸው ረዳ በትግራይ አዲስ የሚቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር በፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ በሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ መመረጣቸው ተነግሯል። የአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ (ቪኦኤ) የትግርኛው አገልግሎት ክፍል እንደዘገበው፣ ጌታቸው የማዕከላዊ ኮሚቴውን አብላጫ ድምጽ አግኝተዋል። የቀድሞው የሕግ መምህር ጌታቸው ረዳ፣ በመንግሥት እና በሕወሓት መካከል በፕሪቶሪያ የሕወሓት  ዋንኛ ተደራዳሪ የነበሩ ናቸው። የሽግግር ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም እየተንቀሳቀሰች የምትገኘው ትግራይ ክልል፣ ከጦርነቱ አስቀድሞ በዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ስትመራ ነበር። ከሰሞኑ በወጡ ዘገባዎች የፌዴራሉ መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ትግራይ በደብረጽዮን መሪነት እንድትቀጥል አይፈልጉም። ዋሺንግተን ፖስት ይዞት በወጣው ዘገባ ዐቢይ ለትግራዩ ጦርነት መጀመር ደብረጽዮንን ይወቅሳሉ። የሕወሓት ሰዎች ከሰላም ስምምነቱ በኋላ…
Read More