ኪነ ጥበብ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባሕል ማዕከል እና ዲኤስቲቪ በመተባበር ያዘጋጁት የጥበብ ምሽት ተካሄደ 

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባሕል ማዕከል እና ዲኤስቲቪ በመተባበር ያዘጋጁት የጥበብ ምሽት ተካሄደ 

"የአንድ ግጥም አንድ ወግ" ኪነ ጥበባዊ ዝግጅት በድምቀት የተከናወነ ሲሆን በዲኤስቲቪ አቦል ቴሌቪዥን የሚተላለፉ ተወዳጅ ድራማዎችን እያቀረቡ ያሉት ተዋናዮችና ፕሮዲዩሰሮች የዝግጅቱ ልዩ እንግዶች በመሆን ልምዳቸውን አካፍለዋል።  የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባሕል ማዕከል ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር ተስፋዬ እሸቱ " በሀገራችን የኪነ ጥበብና በተለይም በቴሌቪዥን ተከታታይ ፊልም ስራዎች ጉልህ አበርክቶ እያከናወነ ካለው ዲኤስቲቪ አቦል ቴሌቪዥን ጋር በትብብር የጥበብ መድረክ ማዘጋጀታችን ወደፊትም ይቀጥላል። ከሌሎች ተባባሪ አካላት ጋርም በትብብር ለመስራት ባሕል ማዕከላችን ክፍት ነው" ሲሉ በመክፈቻ ዝግጅቱ ወቅት ተናግረዋል።  የዲኤስቲቪ ኢትዮጵያ የማርኬቲንግ ኃላፊ ወ/ሮ ትህትና ተስፋዬ በበኩላቸው " እኔ እና ዲኤስቲቪ" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የብራንድ ትውውቅ ከ አአዩ ባሕል ማዕከል ጋር መዘጋጀቱን ገልፀው አብዛኛው…
Read More
ሻኩራ ፕሮዳክሽን የቻይና አምባሳደር ከተሰኘው ተቋም ጋር ስምምነት ፈጸመ

ሻኩራ ፕሮዳክሽን የቻይና አምባሳደር ከተሰኘው ተቋም ጋር ስምምነት ፈጸመ

በካሙዙ ካሳ የተቋቋመው ሻኩራ ፕሮዳክሽን የኢትዮጵያን ባህል ለማስተዋወቅ ከቻይና አምባሳደር ጋር ስምምነት ተፈራርሟል። በቤጂንግ ከተማ የተፈረመው ይህ ስምምነት የኢትዮጵያን ባህል ለማስተዋወቅ ወደ ቤጂንግ ያቀናው "ኢትዮ ኪን" ባህል ቡድን አንድ አካል ነው። በስምምነቱ መሰረት ሁለቱ ተቋማት የኢትዮጵያን እና ቻይናን ባህል፣ ኪነ ጥበብ፣ ትምህርት እና ሌሎች የመልካም ገጽታ ማስተዋወቅ ስራዎችን በጋራ ይሰራሉ ተብሏል። የቻይናው የባህል እና ሚዲያ አገናኝ ኩባንያ ፕሬዝዳንት የሆኑት ሚንግዙ ዛንግ በስምምነቱ ወቅት እንዳሉት "የአባይ ወንዝ መገኛ፣ ቡና መገኛ፣ ታላቅ ህዝብ እና ሀገር የሆነችው ኢትዮጵያ ባህል ለማስተዋወቅ እንፈልጋለን" ብለዋል። "የቻይና ባህል ባለፈው ታሪክ ላይ ብቻ የተመሰረተ አይደለም" ያሉት ፕሬዝዳንቱ ከፈጠራ ጋርም እንደሚያያዝ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም በቀጣይ የጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ…
Read More
አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ መፅሀፍ ተፃፈለት

አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ መፅሀፍ ተፃፈለት

የአትሌት ኃይሌን የህይወትና የስራ ፍልስፍና የሚያስረዳውን መፅሀፍ የፃፈችው ልጁ ሜላት ኃይሌ ገብረስላሴ ናት። ረዳት ፀሀፊው ደግሞ አባዮሚ ሮቲሚ  የተባለ ፀሀፊ መሆኑን ሰምተናል። በ12 ምዕራፍ ተከፋፍሎ የተዘጋጀውን መጽሀፍ ለማሳናዳት ሁለት ዓመት እንደፈጀ ፀሀፊዋ አስረድታለች። አትሌት ኃይሌ ብዙውን የህይወት ታሪኩን ህዝብ የሚያውቀው ቢሆንም መፃህፉ የሚያተኩረው የህይወትና የስራ ፍልስፍናው ላይ እንደሆነ ተነግሯል። ለዚህም ልጁ እንደመሆኗ ከሌሎች ሰዎች በተለየ የአትሌት ሀይሌ ህይወት ለማወቅና ለመፃፍ እንዳስቻላት ሜላት ኃይሌ ጠቅሳለች። መፅሀፉ አትሌት ከእድገቱ እስከ አሁን ባለው የሯጭነትና የቢዝነስ ምዕራፍ የተከተላቸውን አመለካከቶቹን፣ ፍልስፍናውን፣ የህይወት ልምዱ የተካተተበት መሆኑን ልጁ ሜላት ተናግራለች። ለጊዜው ''Dissecting Haile' በሚል ርዕስ ለህትመት የሚበቃው መፅሀፋ ወደፊት ወደ ወደ አማርኛ እና ሌሎች ቋንቋዎች እንደሚተረጎም ተነግሯል።…
Read More
ኢትዮጵያ ለሙዚቀኞች የሮያሊቲ ክፍያ መክፈል ልትጀምር ነው

ኢትዮጵያ ለሙዚቀኞች የሮያሊቲ ክፍያ መክፈል ልትጀምር ነው

የሮያሊቲ ክፍያ ከመጪው ሐምሌ ወር ጀምሮ መክፈል ይጀመራል ተብሏል የሙዚቀኞች የሮያለቲ ክፍያ ከሀምሌ ወር ጀምሮ መክፈል እንደሚጀመር ተገልጿል። መገናኛ ብዙሀን ለሙዚቀኞች የሮያሊቲ ክፍያ እንዲከፍሉ የሚያስገደደው መመሪያ የፊታችን ሀምሌ 1ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል። የሮያሊቲ ክፍያ ረቂቅ መመሪያው የሚመለከታቸው አካላትን ባሳተፈ መንገድ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን  ህጉን ለማስፈጸም ስልጣን የተሰጠው የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ቢበዛ ከአምስት ወር በኃላ ፀድቆ ወደ ስራ እንደሚገባ የባለስልጣኑ ዋና ዳሬክተር አቶ ወልዱ ይመሰል ተናግረዋል። በኢትዮጲያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን አማካኝነት የተሰናደው ይህ ውይይት፣ሙዚቀኞች፣ ፕሮዲውሰሮች፣ደራሲያን እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈውበታል። ውይይቱ በዋናነት በሙዚቀኞች ሮያሊቲ ክፍያ ዙሪያ ያተኮረ ሲሆን ይህንንም ተከትሎ የክፍያ ቀመር  ተዘጋጅቷል። የኢትዮጵያ የቅጅና ተዛማጅ…
Read More
ዝነኛው የኢትዮጵያ ሙዚቀኛ ማሕሙድ አሕመድ ከመድረክ ሊሰናበት ነው

ዝነኛው የኢትዮጵያ ሙዚቀኛ ማሕሙድ አሕመድ ከመድረክ ሊሰናበት ነው

በኢትዮጵያ ከ50 ዓመታት በላይ ከልጅነቱ አንስቶ የአገራችንን ሙዚቃ በተለያዩ የአገራችን ቋንቋዎች በመዝፈን፣ የአገራችንን ሙዚቃ ከአገር አልፎ በአለም አቀፍ ደረጃ እንዲደመጡ ያደረገው ጋሽ ማህሙድ አህመድ ማይኩን ሊሰቅል መሆኑ ተገልጿል፡፡ ማህሙድ ለኢትዮጵያ የሙዚቃ ዕድገት ላበረከተው ከፍተኛ አስተዋጽኦ የጎንደር ዩኒቨርስቲ የክቡር ዶክተር ማዕረግን መስጠቱ የሚታወስ ነው፡፡ በኢትዮጵያ የሙዚቃ ዘርፍ ዝነኛ  የሆነውን የሙዚቃ አባት ከሙዚቃ አለም የመሰናበቻ ፕሮግራም በአዲ አበባ እና በአሜሪካ እንደሚዘጋጅ ተገልጿል፡፡ የመሰናበቻ ሙዚቃ ፕሮግራም ጥር 3 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲ አበባ ሚለኒየም አዳራሽ የድምጻዊ ማሕሙድ አሕመድ የመጨረሻ የህይወት ዘመን ስንብት ደማቅ ኮንሰርት እንደሚዘጋጅ ተነግሯል ፡፡ በዚህ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይም የክቡር ዶ/ር አርቲስት ማሕሙድ አሕመድ የሙዚቃ ሕይወት ላይ የተዘጋጀ መፅሀፍ እንደሚመረቅም ተገልጿል፡፡…
Read More
የአቦል አዳዲስ ይዘቶች ማስተዋወቂያ እና የአፋፍ ቴሌኖቬላ ማጠናቀቂያ ልዩ ዝግጅት ተካሄደ

የአቦል አዳዲስ ይዘቶች ማስተዋወቂያ እና የአፋፍ ቴሌኖቬላ ማጠናቀቂያ ልዩ ዝግጅት ተካሄደ

ሕንድ ለ20 የፊልም ሙያተኞች የስኮላርሽፕ እድል ሰጥታለች “የአቦል አዳዲስ ይዘቶች ማስተዋወቂያና የአፋፍ ቴሌኖቬላ ማጠናቀቂያ” ልዩ በአዲስ አበባ በኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት አዳራሽ (ወመዘክር) ተካሂዷል፡፡ በዚህ መድረክ ላይ ታዋቂ የፊልም ባለሙያዎች፣ ተወናዮች፣ የመንግስት ተቋማት ሃለፊዎች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልመህዲ በፕሮግራሙ ላይ ባደረጉት ንግግር "ዲኤስቲቪ በኢትዮጵያ የፊልም ጥበብ እንዲጎለብት በፋይናንስና በስርጭት እያደረገ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው። በርካቶች የፊልም ጥበብ ባለሙያዎች ይህንን በመጠቀም እየተንቀሳቀሱ ነው" ሲሉ ተናግረዋል። ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለውም ለዚህ ማሳያ የሆነው " አፋፍ ተከታታይ ድራማ በፕሮዳክሽን ጥራትም በይዘትም ምሳሌ በሚሆን መልኩ ተዘጋጅቶ ሲቀርብ ነበር" ብለዋል። በስኬት በመጠናቀቁም የይዘት ባለቤቱን ዲኤስቲቪ አቦል ቴሌቪዥንና አዘጋጁን ሚካኤል…
Read More
ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ “የእልል ያልኩ ሐበሻ” የብራንድ አምባሳደር ሆኖ ተመረጠ

ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ “የእልል ያልኩ ሐበሻ” የብራንድ አምባሳደር ሆኖ ተመረጠ

ወጣቱ ድምፂዊ የሀበሻን ባህላዊ እሴቶችን እንዲሁም ሐበሻ ቢራን እንዲያስተዋውቅ የተመረጠው በሐበሻ ቢራ ፉብሪካ  ነው። በአንድ አልበም እና በተለያዮ ነጠላ ዜማዎች  ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈው  ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ ብራንድ አምባሳደር ሆኖ በመመረጡ የሀበሻ መገለጫ የሆኑ እሴቶች በዓለም አደባባይ ጎልተው እንዲወጡ ይሰራል። "እልል ያልኩ ሀበሻ " በሐበሻ ቢራ አዘጋጅነት የደመቀ ዝግጅት ተካሄዷል። በቃና ዌርሀውስ በተዘጋጀው በአይነቱ ለየት ያለ ፐሮግራም  የኢትዮያዊያን ባሀል፤ ዕሴት፤ማንነት እና ወግ በተለያዩ ክዋኔዎች ባህላዊውን ከዘመነኛው ጋር ያሰናሰኑ ዝግጅቶች ቀርበዋል። በዚህም በምግብ አዘገጃጀት፤በፋሽን ትርዒት፤ በሙዚቃ እና በሌሎች የጥበብ ስራዎች ባሀላዊው ከዘመናዊ ጋር በማሠናሠል ስራ የበረቱ  ባለሞያዎች ስራዎቻቸውን አቅርበዋል። የዝግጅቱ ዓላማም የሀበሻ መገለጫ የሆኑ አለባበሰ፣ምግብ ዝግጅት ፣ሙዚቃ እና የመሳሰሉትን በተለያዩ ሀገረኛ መድረኮች…
Read More
የድምጻዊ ቬሮኒካ አዳነ አዲስ አልበም በ17 ሚሊዮን ብር ተሸጠ

የድምጻዊ ቬሮኒካ አዳነ አዲስ አልበም በ17 ሚሊዮን ብር ተሸጠ

መጠሪያዬ የተሰኘው የድምጻዊ ቬሮኒካ አዳነ አዲስ አልበም በኢትዮጵያ ታሪክ ውዱ አልበም ተብሏል ድምፃዊት ቬሮኒካ አዳነ አዲስ አልበሟ ነሃሴ 23  ለአድማጮች እንደሚደርስ ድምጻዊቷ በዛሬው ዕለት በሰጠችው ጋዜጣዊ  መግለጫ ላይ ተናግራለች። መጠሪያዬ የሚል ስያሜ ያለው ይህ አዲ የሙዚቃ አልበም  የድምጻዊቷ  የመጀመሪያ አልበሟ ሲሆን  አልበሙን ሰርቶ ለማጠናቅ 6 ሚሊዮን ብር እንደፈጀባት ተናግራለች፡፡ በመሆኑም የተጠናቀውን  ሙሉ አልበም በ160ሺ የአሜሪካ ዶላር ወይም ከ17 ሚሊየን ብር በላይ መሸጡን በመግለጫው ለይ ተናግራለች። ይህ ክፍያ በኢትዮጵያ  ታሪክ የመጀመሪያው መሆኑም ተጠቁሟል። አልበሙ በተለያዩ  አማራጮች ለአድማጭ የደረሰ ሲሆን ይህም በቴሌግራም ካሴት መተግበሪያ ላይ ፣ በራሷ የዩቲውብ ቻናል እና በዞጃክ  ዓለም አቀፍ  መተግበሪያዎች ላይ እንደሚለቀቅ ተናግራለች። አልበሙን የገዛው "Zojak worldwide" የተሰኘው የአሜሪካ አሳታሚ ድርጅት…
Read More
የአዲስ አድማስ ጋዜጣ መሥራች ነቢይ መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

የአዲስ አድማስ ጋዜጣ መሥራች ነቢይ መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ መሥራቾች አንዱ የሆነው ገጣሚ፣ ተርጓሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን፣ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ባደረበት ህመም ህክምና ሲከታተል ቆይቶ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም  ረፋዱ ላይ ህይወቱ ማለፉን አዲስ አድማስ ጋዜጣ ዘግቧል። ነቢይ መኮንን ከአዲስ አድማስ መሥራቾች አንዱ የሆነውና በዋና አዘጋጅነት ጋዜጣዋን በመምራት “ተወዳጅ ካደረጓት በቀዳሚነት” ስሙ እንደሚነሳም  በዘገባው ላይ ተጠቅሷል። ነቢይ መኮንን በህትመት ሚዲያ ዘርፍ ዋና አዘጋጅነትን ጨምሮ በርካታ በነበረው አገልግሎት የተለያዩ ስራዎቹን ለአንባቢያን አድርሷል። ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን፤ “ስውር ስፌት” ቁጥር አንድና ሁለት፣ የግጥም መድብሎችን ጨምሮ በርካታ የግጥም ስራዎችን በተለያዩ መድረኮች በማቅረብ ይታወቃል፡፡ “የኛ ሰው በአሜሪካ” የተሰኘ የጉዞ ማስታወሻ መጽሐፉም ተጠቃሽ ስራው ነው፡፡…
Read More
ዲኤስቲቪ በአንጋፋው የአፍሪካ መዝናኛ ፕሮግራም መሪ ኖሎ ሌተሌ ላይ ያተኮረ አዲስ ዘጋቢ ፊልም ሊያሳይ ነው

ዲኤስቲቪ በአንጋፋው የአፍሪካ መዝናኛ ፕሮግራም መሪ ኖሎ ሌተሌ ላይ ያተኮረ አዲስ ዘጋቢ ፊልም ሊያሳይ ነው

አፍሪካ በአለምአቀፍ የብሮድካስት መዝናኛ ኢንደስትሪ ውስጥ ያላትን ቦታ እንዲረጋገጥ ባለፉት 50 ዓመታት የተሰሩ እንቅስቃሲዎች ላይ ትኩረቱን ያደረግውና በተለይም የቀድሞ የመልቲቾይስ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ በመሆን ለረጅመ ጊዜ ያገለገሉት ኖሎ ሌተሌ አስተዋዎ የሚቃኝው አዲስ ዘጋቢ ፊልም “አዎ ለማይቻለው፣ የኖሎ ሌተሌ ታሪከ ” በሚል ርዕስ ተዘጋጀቶ ለእይታ ሊበቃ ነው፡፡  ዘጋቢ ፊልሙ በመላው አፍሪካ ነፃነት ለማግኘት የሚደረጉ እንቅስቃሲዎች በተንሰራፋበት ወቅት በታዳጊ ዕድሚ ላይ የነበሩት ኖሎ አህጉሪቱ የራሷ የሆነ ድምጽ እንዲኖራት የነበራቸውን ራዕይ እንዴት እንደቀረፁት ፣ ይህንንም ራዕይ እውን ለማድረግ ሲያደርጉት የነበረውነ ያላሰለሰ ጥረት እና ረጅም ጉዞ በጥልቀት የሚያስቃኝ ዘጋቢ ፊልም ነው፡፡ በሳውዝሃምፕተን ዩኒቨርሲቲ የኤሌክትሪከ ምህንድስና ትምህርት ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ በዚያን ጊዜ የአፓርታይድ ስርዓት የምትከተለው…
Read More