EthiopianAirlines

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ28 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እንደደረሰበት ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ28 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እንደደረሰበት ገለጸ

ኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በተቋሙ የበጀት አመት አፈጻጸም ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚው ሪፖርቱን ባቀረቡበት ወቅት ጥያቄዎች ተነስተውላቸው ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከነዚህም ጥያቄዎች መካከል ከበረራ ትኬቶች ውድነት ጋር እና አየር መንገዱ በኤርትራ ከተያዘበት ገንዘብ ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ሲሆን ዋና ስራ አስፈጻሚው ምላሽ ሰጥተውበታል። ከሀገር ውስጥ በረራ ጋር በተያያዘ የ28 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እንዳጋጠማቸው ስራ አስፈጻሚው ተናግረዋል። "የዓለም አቀፍ በረራዎች ትኬት ኮምፒውተር ውስጥ በዶላር ነው የተጻፈው ሰው ትኬት ሲገዛ በእለታዊ የዶላር ምንዛሬ ተመን ነው ይህንን ምንም ልናደርግ አንችልም። የሃገር ውስጥ በረራ ግን በብር ነው የተጻፈው ባለፈው አመት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ወቅት አልጨመርንም የዶላር…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ14 ሚሊዮን በላይ መንገደኞች ማጓጓዙን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ14 ሚሊዮን በላይ መንገደኞች ማጓጓዙን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት 9 ወራት 14.5 ሚሊዮን መንገደኞችን ማጓጓዙን አስታውቋል፡፡ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲመሳከር የ13 በመቶ እድገት እንዳለው ዋና ስራ አስፈፃሚው መስፍን ጣሰው ተናግረዋል፡፡ አየር መንገዱ በዘጠኝ ወር ውስጥ ያገኘው ገቢ 5.6 ቢሊዮን ዶላር መሆኑንን የተናገሩት አቶ መስፍን ጣሰው ገቢውም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲተያይ የ8 በመቶ ብልጫ አሳይቷል ብለዋል፡፡ በጊዜ ማዕቀፍ 10 አዳዲስ አውሮፕላኖች የኢትዮጵያ አየር መንገድን መቀላቀላቸው የተጠቀሰ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ሶስቱ ኤርባስ A350-1000 መሆናቸው ተሰምቷል፡፡ በዘጠኝ ወሩ ውስጥ አራት አዳዲስ የበረራ መዳረሻዎችንም የኢትዮጵያ አየር መንገድ መክፈቱን ጠቅሷል፡፡ አየር መንገዱ የፊታችን እሁድ ጁን 1, 2025 ከአዲስ አበባ ወደ ተባበሩት አረብ ኢምሬት ሻርጃህ ከተማ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ መብረር አቆመ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ መብረር አቆመ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባወጣው መግለጫ ከነገ ነሀሴ 28 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን በረራ እንደሚያቆም አስታውቋል፡፡ ከአዲስ አበባ ወደ አስመራ እና ከአስመራ ወደ አዲ አበባ የሚደረጉ በረራዎችን አቋርጫለሁ ያለው አየር መንገዱ በኤርትራ ያለው አሰራር አስቸጋሪ እና ከቁጥጥሩ ውጪ መሆኑ ለበረራው መቋረጥ በምክንያትነት ተጠቅሷል፡፡ ጉዞ ለማድረግ ቲኬት የገዙ መንገደኞችም በመረጡት አየር መንገዶች እንዲበሩ እንደሚያደርግ እና የዋጋ ጭማሪ እንደማያደርግም አየር መንገዱ ገልጿል፡፡ ኤርትራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ከመስከረም 30 በኋላ ወደ አስመራ እንዳይበር መከልከሏ ይታወሳል፡፡ የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ከአንድ ወር በፊት ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አስመራ በሚጓዙ ተጋዦች ላይ “የተደራጀ እና ስልታዊ የሻንጣ ስርቆት፣ ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ፣…
Read More
በአዲስ አበባ ያለው ከባድ አየር ንብረት የአውሮፕላን በረራዎችን አስተጓጎለ

በአዲስ አበባ ያለው ከባድ አየር ንብረት የአውሮፕላን በረራዎችን አስተጓጎለ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዲስ አበባ በተከሰተው ከፍተኛ ጭጋጋማ አየር ምንክንያት ወደ ሌላ አየር ማረፊያዎች እያዘዋወረ መሆኑን አስታወቀ በአዲስ አበባ በተከሰተዉ ከፍተኛ ጭጋጋማ አየር አብዛኛው በረራዎች ቦሌ አዉሮፕላን ማረፊያ ሊያርፍ ባለመቻሉ ምክንያት ወደ ሌላ አየር ማረፊያዎች እንዲቀየሩ መደረጉን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል ። አየር መንገዱ እንደገለፀው ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ባለዉ ከፍተኛ ጭጋግ ( ጉም) ምክንያት የአየር ማረፊያዎችን ወደ ሌላ ቦታ እያዘዋወረ መሆኑን እና ይህም በሀገር ዉስጥ እና በአለም አቀፍ በረራዎች ላይ ተፅዕኖ አሳድሯል ብሏል። በተጓዦች ላይ ለደረሰዉ መጉላላት ይቅርታ የጠየቀው አየር መንገዱ በተጓዦች ላይ ሊደርሱ የሚችሉ መጉላላቶችን ለመቀነስ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ አውሮፕላን ጣቢያ…
Read More
ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የኢትዮጵያ አየር መንገድን ሸለሙ

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የኢትዮጵያ አየር መንገድን ሸለሙ

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የህይወት ዘመን ሽልማት አበርክተዋል። የዓለማችን ልዕለ ሀያል ሀገር የሆነችው አሜሪካ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የህይወት ዘመን ሽልማት አበርክታለች። ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለአሜሪካዊያን አገልግሎት የሰጡ ተቋማትን እና ግለሰቦችን የህይወት ዘመን ሽልማት ይሰጣል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት 25 ዓመታት በአሜሪካ ለሚኖሩ ዜጎች በሰጠው አገልግሎት የህይወት ዘመን ተሸላሚ ሆኗል። አየር መንገዱ ሽልማቱን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ "ሽልማቱ ለሰጠው አገልግሎት እውቅና የሰጠ ነው" ብሏል። ፕሬዝዳንት ባይደን የፈረሙበት ይህ ሽልማት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመራሮች በአትላንታ በተዘጋጀ መርሀግብር ላይ ተቀብለዋል ተብላል። የአየር መንገዱ ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ሽልማቱ ባለፉት ዓመታት ለሰጠው የአቪዬሽን አገልግሎት እውቅና ባለፈ ዓለም አቀፍ ትብብሮችን እንዲያሰፋ…
Read More
ኤርትራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሀገሯ እንዳይበር አገደች

ኤርትራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሀገሯ እንዳይበር አገደች

የኢትዮጵያ አየር መንገድ “ከመስከረም ወር ጀምሮ አየር መንገዳችን ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን ሁሉንም በረራ ማገዱን አሳውቆናል” ብሏል፡፡ ኤርትራ የትራንስፖርት እና ኮሚዩኒኬሽን ሚኒስቴር የሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን የኤርትራ መንግሥት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቀጣዩ መስከረም በኋላ ወደ አሥመራ እንዳይበር ማገዱን የሚያሳውቅ ማስታወቂያ በዛሬው እለት አውጥቷል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይህንን አስመለክቱ በሰጠው መግለጫ፤ “የኤርትራ የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ሐምሌ 14 2016 ዓ.ም ወይም በፈረንጆቹ 21 ጁላይ 2024 በላከው ደብዳቤ በፈረንጆቹ ከመስከረም 30 ቀን 2024 ዓ.ም. ጀምሮ አየር መንገዳችን ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን ሁሉንም በረራ ማገዱን አሳውቆናል” ብሏል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጉዳዩን አስመልክቶ የኤርትራ የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣንን ለማግኘት ጥረት በማድረግ ላይ እንደሚገኝና ጉዳዩም በበጎ መልኩ እልባት እንደሚያገኝ ያለውን…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ50 ሚልየን ዶላር ያስገነባውን የመንገደኞች ማስተናገጃ አስመረቀ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ50 ሚልየን ዶላር ያስገነባውን የመንገደኞች ማስተናገጃ አስመረቀ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በ50 ሚልየን ዶላር ያስገነባውን አዲስ የአገር ውስጥ መንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል ዛሬ አስመረቀ። በአየር መንገዱ ከአዲስ አበባ ወደ ሁሉም የአገር ውስጥ መዳረሻዎች እንዲሁም ከአገር ውስጥ ወደ አዲስ አበባ ለሚደረጉ በረራዎች በዚህ ተርሚናል አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው አዲሱ የአገር ውስጥ ተርሚናል አየር መንገዱ የሚሰጠውን የአገር ውስጥ በረራ አቅም በዕጥፍ እንደሚያሳድገው አስታውቀዋል። አየር መንገዱ 22 የአገር ውስጥ መዳረሻዎች አሉት። የቱሪዝም ሚኒስትሯ አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ አዲስ የተገነባው የአገር ውስጥ ተርሚናል የቱሪዝም ዘርፍ በማሳደግ በኩል ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ገልጸዋል። አየር መንገዱ ከሁለት ወራት በፊት በ55 ሚሊዮን ዶላር ያስገነባውን የድጅታል ግብይት…
Read More
ሶማሊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በግዛቷ እንዳያርፍ ከለከለች፡፡

ሶማሊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በግዛቷ እንዳያርፍ ከለከለች፡፡

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና በራስ ገዟ ሶማሊላንድ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሄ አብዲ ከሶስት ሳምንት በፊት በአዲስ አበባ የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸው ይታወሳል። ስምምነቱ ኢትዮጵያ በኤደን ባህረ ሰላጤ 20 ኪሎሜትሮች የሚረዝም የባህር ጠረፍ እንድትከራይ እና በምትኩ ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና እንድትሰጥ የሚያስችል ነው። ይህ ስምምነት ሶማሊላንድን የራሷ ሉአላዊ ግዛት አድርጋ በምታያት ሶማሊያ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል። ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ የበረራ ቁጥሩ ET8372 የተሰኘ አውሮፕላን ወደ ራስ ገዟ ሶማሊላንድ በዛሬው ዕለት በረራ በማድረግ ላይ እያለ እንዲመለስ መደረጉ ተገልጿል፡፡ የሶማሊያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን በቀድሞ ስሙ ትዊተር አሁን ኤክስ አካውንቱ ይፋ እንዳደረገው የግዛቴ አካል ናት ወደ ሚላት ሶማሊላንድ ሀርጌሳ እየበረረ የነበረ አውሮፕላን እንዳያርፍ…
Read More
የኢትዮጵ አየር መንገድ ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ ጀመረ

የኢትዮጵ አየር መንገድ ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ ጀመረ

አየር መንገዱ በአፍሪካ ያሉትን የጭነት መዳረሻዎች ብዛት ወደ 35 አሳድጓል። ወደ ካዛብላንካ የሚደረገው የጭነት በረራ ከ100 ቶን በላይ የመሸከም አቅም ባለው ቦይንግ 777-200F የእቃ ጭነት አውሮፕላን ነው ተብሏል። የኢትዮጵ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው “ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ አገልግሎት መስጠት በመጀመራችን ደስታ ተሰምቶናል ብለዋል በመልዕክታቸው። ይህ በረራ መጀመሩ በአፍሪካ ያለንን የዕቃ ጭነት መዳረሻ ቁጥር 35 ሲያደርስ፤ በተመሳሳይ ብሔራዊ አየር መንገዱ በእቃ ጭነት አገልግሎት ዘርፍ አስተማማኝ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በጭነት በረራ መዳረሻዎች ብዛት ከአፍሪካ ቀዳሚ እና በዓለም የአየር የዕቃ ጭነት አገልግሎት መስክ ቁልፍ ሚና በመጫወት ላይ የሚገኝ…
Read More
ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉዞ ቲኬት በብድር መሸጥ ጀመሩ

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉዞ ቲኬት በብድር መሸጥ ጀመሩ

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኞች የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቅመው ክፍያውን ቆይተው የሚከፍሉበትን አዲስ የክፍያ አማራጭ በጋራ አስተዋውቀዋል። አቶ ዮሃንስ ሚሊዮን የዳሽን ባንክ ዲጂታል ባንኪንግ ዋና መኮንን “ጉዞዎ ይቀድማል ክፍያው ይደርሳል” በሚል የተሰየመው ይህ አገልግሎት በደንበኞች ምርጫ መሰረት በ6 ወር ወይም በ12 ወር የብድር ክፍያ የሚሰጥ መሆኑን አመልክተዋል። ደንበኞች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን በዳሸን ባንክ የሂሳብ ቁጥር መክፈት እንደሚገባቸው እና በተጨማሪም በባንኩ ቢያንስ ለሶስት ወራት አገልግሎት ያገኙ መሆን እንደሚኖርባቸውም ጠቁመዋል።  አቶ ዮሃንስ አክለውም አገልግሎቱን ለማግኘት ደንበኞች አቅራቢያቸው ወደሚገኝ የዳሸን ባንክ ቅርንጫፍ በሚያመሩበት ወቅት አስፈላጊ ሰነዶችን ማሟላት የሚገባቸው ሲሆን ማስያዣም ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸውም ገልፀዋል። ስምምነቱን አስመልክቶ የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና…
Read More