Courtreporting

በህገወጥ መንገድ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ዱባይ ሲልክ የነበረው ሰው በ20 ዓመት እስራት ተቀጣ

በህገወጥ መንገድ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ዱባይ ሲልክ የነበረው ሰው በ20 ዓመት እስራት ተቀጣ

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ወረዳ  ቢቂላ ከተማ ውስጥ ነዋሪ የሆነው ግለሠብ ከሚመለከተው አካል እውቅና ፈቃድ ሣያገኝ ሰዎችን ወደ ዱባይ የሚልከው ግለሠብ በእስራት መቀጣቱን ፖሊስ አስታዉቋል። የምዕራብ አርሲ ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ የወንጀል ምርመራ ክፍል ሐላፊ ዋና ኢንስፔክተር ከድር ጅቦ እንደተናገሩት ተከሣሽ ገመቹ  ሰይድ የተባለው ግለሠብ ከሚመለከተው አካል እውቅና ፈቃድ ሣይኖረው  በዶዶላ ወረዳ ቢቂላ ከተማ ነዋሪ የሆኑ ሁለት ግለሠቦችን ከፍተኛ የስራ ልምድና ችሎታ  ስላላችሁ ስራ የማግኘት እድላችሁ ሰፊ ነው በማለት የማታለያ ቃል በመጠቀም ወደ ዱባይ እንደላካቸው ገልፀዋል። ተከሣሹ የተለያዩ  አሣማኝና  ማታለያ ቃላቶችን በመጠቀም ከሁለቱ ግለሠቦች 250 ብር በአጠቃላይ 500 ሺህ ብር በመቀበል ወደ ተባበሩት አረብ ኢምሬት ዱባይ ከተማ የላካቸው መሆኑ…
Read More
የቀድሞው ጉምቱ ባለስልጣን የ13 ዓመት እስር ተፈረደባቸው

የቀድሞው ጉምቱ ባለስልጣን የ13 ዓመት እስር ተፈረደባቸው

የቀድሞው የአደጋ ስጋት ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ በሙስና ወንጀል በ13 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጡ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የቀድሞ ኮሚሽነር የነበሩት አቶ ምትኩ ካሳ በከባድ የሙስና ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በ50 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል። የፍትሕ ሚኒስቴር ዐቃቤ ሕግ ባቀረበው ክስ፣ አቶ ምትኩ ከሌሎች ተባባሪዎች ጋር በመሆን የተረጂዎችን ቁጥር በማጋነን ከ601 ሺህ ኩንታል በላይ ስንዴን ጨምሮ በርካታ የምግብ እርዳታ ቁሳቁሶችን ከመጋዘን በማውጣት ለተረጂዎች ሳይደርስ ለዱቄት ፋብሪካዎችና ለሌሎች በመሸጥ ለግል ጥቅማቸው እንዳዋሉ አስረድቷል። በተጨማሪም፣ ከ472 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ገንዘብ በሕገ ወጥ መንገድ እንዲከፈል በማድረግ በመንግስት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ…
Read More
በሽብር ወንጀል የተከሰሱ ጋዜጠኞች የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቆ ሆኖ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ተወሰነ

በሽብር ወንጀል የተከሰሱ ጋዜጠኞች የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቆ ሆኖ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ተወሰነ

አራት የመገናኛ ብዙሃን ጋዜጠኞች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ በፍርድ ቤት ውድቅ ተደረጓል። በሽብር ወንጀል የተከሰሱ አራት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች እና ሌሎች 19 ተከሳሾች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ፤ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውድቅ ተደረገ። የተከሳሾችን በቁጥጥር ስር መዋል በተመለከተ የጸጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ያወጣውን መግለጫ በድረ ገጻቸው የጫኑ መገናኛ ብዙሃን ዘገባዎቻቸውን እንዲያወርዱም ፍርድ ቤቱ አዝዟል። ይህን ትዕዛዝ የሰጠው ሐምሌ 12 ቀን 2015 ዓ.ም የዋለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ችሎት ነው። ችሎቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጎ ትዕዛዞችን በሰጠበት ቅጽበት ተከሳሾች በጭብጨባ የታጀበ መፈክር አሰምተዋል። የተከሳሾቹ መፈክር እና ጭብጨባ፤ የችሎት ውሎ…
Read More
እነ ዶክተር ሙሉቀን ሀብቱ ከተከሰሱበት የሙስና ወንጀል በነጻ ተሰናበቱ

እነ ዶክተር ሙሉቀን ሀብቱ ከተከሰሱበት የሙስና ወንጀል በነጻ ተሰናበቱ

ዶ/ር ሙሉቀን ሐብቱን ጨምሮ ከጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ክስ የተመሰረተባቸው አምስት ግለሰቦች በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነጻ ተባሉ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀድሞው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክ ሙያና ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉቀን ሐብቱን ጨምሮ ከጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው አምስት ግለሰቦች በነጻ አሰናብቷቸዋል፡፡  ፍርድ ቤቱ ብይኑን የሰጠው ዛሬ ረቡዕ ሚያዚያ 4፤ 2015 በዋለው ችሎት ነው፡፡  በዚሁ መዝገብ ክስ ከቀረበባቸው ግለሰቦች መካከል አንድ ተከሳሽ በሌሉበት ጥፋተኛ ሲባሉ፤ ቀሪ አምስት ተከሳሾች ደግሞ የተከሰሱበት ድንጋጌ ተቀይሮ እንዲከላከሉ በፍርድ ቤቱ በይኗል። ችሎቱ አምስት ተከሳሾችን በነጻ ያሰናበተው፤ “ዐቃቤ ህግ ባቀረበው የሰው…
Read More