ነፃ አስተያየት

የ”ዲጂታል ይዘት ስርቆት” እና ችላ የመባሉ አስጊ ተፅዕኖዎች

የ”ዲጂታል ይዘት ስርቆት” እና ችላ የመባሉ አስጊ ተፅዕኖዎች

በደመቀ ከበደ በኢትዮጵያ የፈጠራና የባህል ኢኮኖሚ ላይ የተጋረጠው የ"ዲጂታል ይዘት ስርቆት" እና ችላ የመባሉ አስጊ ተፅዕኖዎች በአዲስ አበባ እምብርት ውስጥ ወጣት የሙዚቃ አቀናባሪዎች የሙዚቃ ገበያውን ዓለም ሊያነቃንቁ የሚችሉ ቅኝቶችን ሲያመርቱ ይውላሉ። ፊልም ሰሪዎቻችን የኢትዮጵያን ማንነትና ነፍስ የሚዘክሩ ታሪኮችን በካሜራቸው ይስላሉ። በከተማዋ በሚገኙ የሲኒማቶግራፊ ስቱዲዮዎች እና የዲጂታል አማራጮች ውስጥም የሀገር በቀል ታሪኮችን ከዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃ ጋር ያዋሃዱ የሚዲያ ስራዎች ለመፍጠር እየታተሩ ነው። በሽሮ ሜዳ የእጅ ባለሙያዎችም የዘመናት ቅርስ የሆነውን የጋሞን ጥበብና ድንቅ ድሮችን ወደ ዘመናዊ ገበያ እያመጡ ነው። በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ የሰርከስ ተሳታፊዎችና የውዝዋዜ ቡድኖች ጥንታዊ ትውፊትን ከዘመናዊ ፈጠራ ጋር አዋህደው ልምምዳቸውን ያደርጋሉ። ከሶፍትዌር አልሚዎችና ዲዛይነሮች እስከ ጸሐፍትና የሶሻል…
Read More
ጊቭ ዋተር ከ200 ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የንጹህ መጠጥ ውሀ ማቅረቡን ገለጸ

ጊቭ ዋተር ከ200 ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የንጹህ መጠጥ ውሀ ማቅረቡን ገለጸ

ሀገር በቀሉ ጊቭ ዋተር የተሰኘው ድርጅት ከ31 ሚሊዮን ብር በላይ ሃብት በማሰባሰብ ከ200 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያንን ንጹህ የመጠጥ ውሀ ተጠቃሚ ማድረጉን አስታውቋል። የድርጅቱ ሀብት ማሰባሰብ ኃላፊ አቶ ከማል አህመድ እንዳሉት ድርጅቱ ከተመሰረተበት 2010 ጀምሮ ላለፉት 15 ዓመታት በንፁህ የመጠጥ ውሃ እጦት ክፉኛ እየተፈተኑ ላሉ የገጠር ማህበረሰብ አካባቢዎች የተለያዩ እና በርካታ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ህበረተሰቡን ተጠቃሚ መደረጉን ገልፀዋል። ጊቭ ዎተር በ15 ዓመታት የልማት ጉዞው የሰው ልጅ መሰረታዊ ፍላጎቶች መካከል አንዱ በሆነው የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ዘርፍ የገጠሩን ማህበረሰብ የትኩረት ማዕከሉ በማድረግ ሲንቀሳቀስ ቆይቷልም ብለዋል። ድርጅቱ በተጠቀሱት ዓመታት ውስጥ ከ31 ሚሊዮን ብር በላይ ሃብት በማሰባሰብ በ 7 ክልሎች በተለይም በአፋር፣ ሶማሌ፣…
Read More
“ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል”

“ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል”

በክቡር ገና በሀገራችን “ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል” የሚል ምሳሊያዊ አነጋገር አለ፡፡ አጋም እሾሀማ ተክል ሲሆን ቁልቋል ደግሞ ለመወጋት የተመቸ ጠፍጣፋ ቅጠል መሰል አካል ያለው ተክል ነው፡፡ አጋሙ በጠንካራ እሾሁ ቁልቋሉን ሲወጋው ልክ ህመሙ ያሰቃየው ይመስል ከጠፍጣፋ አካሉ እንደ እንባ ነጭ ፈሳሽ ያነባል፡፡ እናም “ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል” የተባለውም ለዚህ ነው፡፡ ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ እንደሚኖር ሁሉ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) የተጠጋም ሀገር ያለጥርጥር ሲያለቅስ ይኖራል፡፡ ከአይ ኤም ኤፍ ተጠግተው ሲያለቅሱ የኖሩ በርካታ ሀገራትን መጥቀስ ቢቻልም አርጀንቲና፣ ግብጽ፣ ናይጄሪያና ዛምቢያ ጥሩ ማሳያዎች ናቸው፡፡ አሁን ደግሞ ተራው የኢትዮጵያ ነው፡፡ በቅርቡም የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጂዎሪጄቫ ኢትዮጵያን ጎብኝተው “ በአዲስ…
Read More
እየሰጡ መንሳት

እየሰጡ መንሳት

በበፍቃዱ ኃይሉ ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚኒስትርነት ከኃይለማርያም ደሳለኝ ከተረከቡ ስድስት ዓመታት ተቆጠሩ። ዐቢይ በእነዚህ ዓመታት የተከተሉት የአመራር ሥልት በፍቃዱ ኃይሉ “እየሰጡ መንሳት” የሚለው አባባል ይገልጸዋል የሚል አተያይ አለው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያን የሥልጣን ማማ ከተቆናጠጡ እነሆ ዛሬ መጋቢት 24፣ 2016 ስድስት ዓመት ሞላቸው። በዘመናዊ ፖለቲካ ከአንድ የአገር መሪ የሚጠበቁት መሠረታዊ ኃላፊነቶች ሰላም እና መረጋጋት ማስፈን፣ ሕግ እና ስርዓት ማበጀት እንዲሁም ሥራ መፍጠር እና ኢኮኖሚ ማረጋጋት ናቸው። እነዚህ ዘርፎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እምብዛም ናቸው። ይልቁንም በነውጥ እና ወጀብ እየተላጋች በምትሔደው መርከብ ውስጥ ወደ ካፒቴኑ መንበር ለመውጣት እርካቡ ላይ መንጠላጠል እንዲሁም መንበሩ ላይ ተደላድሎ መቀመጥ ግን ይችሉበታል። ይህንን…
Read More
ጦርነት እና እግር ኳስ በኢትዮጵያ….

ጦርነት እና እግር ኳስ በኢትዮጵያ….

ቢኒያም ተክለወይኒ እባላለሁ። ትውልዴ ሽረ ነው። ከጦርነቱ በፊት የፕሪሚየር ሊጉ ተካፋይ የሆነው የስሑል ሽረ ዋና ቡድን ተጨዋች ነበርኩ ። ሊብሮ ነኝ ። አሰልጣኝ ዳንኤል ፀሐዬ ዋና አሰልጣኛችን ነበር ። ኳስ እወዳለሁ ። ደጉ ደበበን አደንቃለሁ ። እንደ እርሱ የመሆን ምኞት ነበረኝ ። ተቀራኒ ሆነን ተጫውተናልም:: በኳስ ጨዋታ መከላከልን እወዳለሁ ። አዳነ ሳላ አማኑኤልን ጨምሮ ከብዙ ጎበዝ አጥቂዎች ተፋጥጫለሁ ። ሁሉንም ገትሬ አቁሜያለሁ ። ቡድኔ ጎል እንዳይቆጠርበት በአግባቡ መምራት መከላከል ከስሑል ሽረ ጋር በፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን መሆን የዘወትር ህልሜ ነበር ። ከሽረ ውጭ ሌላ ክለብ አላውቅም ። በኳስ ጨዋታ መንገዴ የእራሴንም የቤተሰቦቼንም ህይወት መቀየር ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተመርጦ መጫወት የሌት ተቀን…
Read More
የኢትዮጵያ አቪየሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ አደገ

የኢትዮጵያ አቪየሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ አደገ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቪዬሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ በማደግ በኤሮስፔስ እና በተለያዩ የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፎች በቅድመ ምረቃ እና ድሕረ ምረቃ ፕሮግራሞች ማስተማር ጀመረ። የአቪዬሽን አካዳሚ የአቪዬሽን ስልጠና ፕሮግራሞችን በአብራሪነት፣ የአውሮፕላን ቴክኒሻን፣ የካቢን ሰራተኛ፣ የአየር መንገድ ሽያጭ እና አገልግሎት እና ሌሎች ስልጠናዎችን ሲሰጥ ቆይቷል።  ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ ካደገ በኋላ በኤሮኖቲካል ኢንጂነሪንግ በቢኤስሲ ዲግሪ፣ በአውሮፕላን ጥገና ኢንጂነሪንግ በቢኤስሲ ዲግሪ፣ በአቪዬሽን ማኔጅመንት ቢኤስሲ ዲግሪ፣ በቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ማኔጅመንት ቢኤ ዲግሪ እና ኤምቢኤ በአቪዬሽን ማኔጅመንት የመሳሰሉ የዲግሪ መርሃ ግብሮችን ጀምሯል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው እንደተናገሩት "ከቀጣይ እድገትና ኢንቨስትመንት በኋላ 65 ዓመት ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ ማደጉ…
Read More