orthodoxchurch

መንግስት በኦሮሚያ ክልል አርሲ በቂ የጸጥታ ሀይል እንዲያሰማራ ኢሰመኮ ጠየቀ

መንግስት በኦሮሚያ ክልል አርሲ በቂ የጸጥታ ሀይል እንዲያሰማራ ኢሰመኮ ጠየቀ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ንጹሃን ዜጎች ግድያ እንደተፈጸመባቸው አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ ኮሚሽኑ በሪፖርቱ ላይ እን ዳስታወቀው በዞኑ ያለው ሁኔታ ለተወሰኑ ጊዜያት እየተሻሻለ የነበረ ቢመስልም ከጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም ጀምሮ ታጣቂ ቡድኑ በሽርካ፣ በጉና፣ በመርቲ፣ በአሰኮ እና በኦንቆሌ ዋቤ ወረዳዎች በሰዎች ላይ በፈጸማቸው ጥቃቶች በሰዎች ሕይወት፣ አካልና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ገልጿል፡፡ እንዲሁም ከዚሁ ጋር በተያያዘ በተፈጠሩ የደህንነት ሥጋቶች ምክንያት የነዋሪዎች መፈናቀል መከሰቱን ኢሰመኮ የደረሱትን ጥቆማዎችና አቤቱታዎች መሠረት በማድረግ የተጎጂ ቤተሰቦችን፣ ነዋሪዎችን እና የየአካባቢዎቹን የመንግሥት ኃላፊዎች በማነጋገር ባሰባሰባቸው መረጃዎች ማረጋገጡን አስታውቋል። የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (በተለምዶ “ኦነግ ሸኔ”) የካቲት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በዞኑ ሽርካ ወረዳ ጃዊ…
Read More
ቋሚ ሲኖዶሱ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የተፈጸመውን የ25 ምዕመናን ግድያ አወገዘ

ቋሚ ሲኖዶሱ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የተፈጸመውን የ25 ምዕመናን ግድያ አወገዘ

በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ አርሲ ዞን አስተዳደር በጉና፣ በመርቲ፤ በሸርካ እና በሆሎንቆ ዋቢ ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች ላይ ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች የተፈጸሙትን አሰቃቂ ግድያዎች የቤተክርሲቲያኒቷ ቋሚ ሲኖዶስ አውግዟል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖችን አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል፡፡ በመግለጫውም ጥቅምት 14 ለ15 ቀን 2018 ዓ.ም በጉናና መርቲ ወረዳዎች 17 ክርስቲያኖች፣ ጥቅምት 17 ለ18 ቀን 2018 ዓ.ም. በሸርካ ወረዳ 3 ክርስቲያኖች እንዲሁም ጥቅምት 18 ለ19 ቀን 2018 ዓ.ም. በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 5 ክርስቲያኖች በድምሩ በጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም. ብቻ 25 ኦርቶዶክሳውያን በድንገት ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን አስታውቋል፡፡ ግድያውም…
Read More
ቤተ ክርስቲያኗ በትግራይ ክልል ያሉ የአራት ሊቀ ጳጳስን ክህነት አነሳች

ቤተ ክርስቲያኗ በትግራይ ክልል ያሉ የአራት ሊቀ ጳጳስን ክህነት አነሳች

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትግራይ ክልል የተሰጠው ኤጲስ ቆጵሳት ሹመት ህገወጥ መሆኑን አስታውቃለች። የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ በተፈጠረው ወቅታዊ የዶግማ፣ የቀኖናና የአስተዳደራዊ ጥሰቶችን አስመልክቶ ውሳኔዎች አሳልፌያለሁ ብሏል። ቤተ ክርስቲያኗ አክላም ከፍተኛውን ሐዋርያዊ ተልእኮ እንዲወጡ አደራ በተሰጣቸው ሊቃነ ጳጳሳት በማኅበረሰብ ዕድገትና አስተዳደር ውስጥ ከሕዝብ ጋር በቆመች፣ ከፖለቲካ በጸዳች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ መንፈሳዊና ሕዝባዊት ተቋምነቷን በመካድ ከፍተኛ የሆነ ሕገ ወጥ ድርጊትና ተቋምን የመናድ እንደሁም መዋቅሯን የማፍረስ ተግባር ተከናውኖብኛል ብላለች። ሐምሌ 16 እና 23 ቀን 2015 ዓ/ም በክልል ትግራይ በማእከላዊ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ማርያም ገዳም ውስጥ የተፈጸመውን ሕገወጥ የሆነ አስነዋሪ፤ የቀኖና ቤተ…
Read More
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የትግራይ ህዝብን ይቅርታ ጠየቀች

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የትግራይ ህዝብን ይቅርታ ጠየቀች

ቤተ ክርስቲያኗ ዘጠኝ ኤጲስ ቆጶሳትን እንደምትሾም አስታውቃለች ቤተክርስቲያኗ ባወጣችው መግለጫ ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጭ በተፈጸመው ሲመት በቤተ ክርስቲያኒቷ ላይ የደረሰውን መከራና ፈተና ለማሳለፍ ሲባል ዶግማዋን፣ ቀኖናዋን እና ትውፊቷን ባስጠበቀ ሁኔታ ችግሩ በውይይት እንዲፈታ ትረት ስታደርግ መቆየቷን ገልጻለች። በዚህ መሰረትም የካቲት 8 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠቅላይ ሚኒስቴር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በተደረሰው ስምምነት መሠረት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ቀኖናዋን ከስምምነቱ ፤ ስምምነቱን ከቀኖናዋ ጋር በማዛመድ በኦሮሚያ እና በደቡብ ክልል ባሉ ክፍት አህጉረ ስብከት ተመድበው የሚያገለግሉ 9 ኤጲስ ቆጶሳት በቀኖና ቤተ ክርስቲያን እንዲሾሙ…
Read More
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን የ23 የቀድሞ አባቶችን ውግዘት አነሳች

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን የ23 የቀድሞ አባቶችን ውግዘት አነሳች

ቤተ-ክርስቲያኒቱ ከህግ ውጭ ሲመተ ጵጵስና የሰጡና የተቀበሉ 26 የቀድሞ አባቶችን ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ማውገዟ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የሦስት ጳጳሳትንና የ20 መነኮሳትን ውግዘት አንስቷል። ውግዘቱ የተነሳው ከዛሬ መጋቢት 21፤ 2015 ዓ.ም. ጀምሮ እንደሆነ ምልዓተ ጉባኤው አሳውቋል። ቅዱስ ሲኖዶስ በመግለጫው "ሦስቱም የቀድሞ ሊቃነ ጳጳሳት ማለትም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ እና ብፁዕ አቡነ ዜናማርቆስ ላይ የተላለፈው ውግዘት ከዛሬ መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ተነስቷል" ብሏል፡፡ በቀድሞ የሊቀ ጳጳስነት ማዕረጋቸው እንዲጠሩና ተመድበው ይሰሩበት በነበረው የስራ ኃላፊነታቸው እንዲቀጥሉም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ የየካቲት ስምንቱን ባለ10 ነጥብ ስምምነት እንቀበላለን ብለው ለቅዱስ ሲኖዶስ ደብዳቤ ያስገቡ 20 የቀድሞ አባቶች ውግዘትም…
Read More