FederalPolice

ፖሊስ ከሶስት ባንኮች 89 ሚሊዮን ብር ያጭበረበረውን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለጸ

ፖሊስ ከሶስት ባንኮች 89 ሚሊዮን ብር ያጭበረበረውን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለጸ

በሶስት ባንኮች ላይ የ89 ሚሊዮን ብር ምዝበራ የፈጸመው ቡድን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል። ፖሊስ ዛሬ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ በሐሰተኛ የባንክ ዋስትና ሰነድ በመጠቀም በገዳ ባንክ፣ በኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል የፈጸሙ ተጠርጣሪዎችን ከነግብረ-አበሮቻቸው በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታውቋል። ተጠርጣሪዎቹ በተቀነባበረ ሴራ በአጠቃላይ ከ89 ሚሊዮን 296 ሺህ ብር በላይ በሀገር ኢኮኖሚ እና በባንኮች ላይ ጉዳት አድርሰዋል ተብሏል። ተጠርጣሪው የጎደር ዋይን ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ ጌታሁን መለስ ሲሆን፣ ከገዳ ባንክ አገምሳ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አብዲሳ ቶሎሳ ጋር በጥቅም በመመሳጠር የቅርንጫፉን ፊርማና ማህተም ለወንጀል ተግባራቸው ሲጠቀሙበት መቆየታቸው ተገልጿል። ዋነኛው ተጠርጣሪ…
Read More
ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ ተጠርጣሪ ኢትዮጵያዊያን ተላልፈው እንዲሰጧት ጠየቀች

ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ ተጠርጣሪ ኢትዮጵያዊያን ተላልፈው እንዲሰጧት ጠየቀች

ኢትዮጵያ በወንጀል የምትፈልጋቸውን ሰዎች አሜሪካ አሳልፋ እንድትሰጣት ጥያቄ አቅርባለች፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ  ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ጋር ተወያይተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከአሜሪካው ኤፍ.ቢ.አይ (FBI) ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር አምባሳደሩ የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ኮሚሽነሩ በውይያታቸው ወቅት ጠይቀዋል ተብሏል፡፡ ኢትዮጵያ በተለይም በአሜሪካን ሀገር እየኖሩ የሀገሪቱን ሰላም እያወኩ ነው በሚል የምትጠረጥራቸውን ሰዎች ተላልፈው እንዲሰጧት ለአምባሳደሩ ጥያቄ እንዳቀረቡም ተገልጿል፡፡ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በአሜሪካን መንግሥት የሚፈለጉ ወንጀለኞችን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አሳልፎ በመስጠት ላበረከተው አስተዋፅኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ተብሏል፡፡ አምባሳደሩ አክለውም ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ተመሳሳይ ድጋፎችን እንድታደርግ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል ሲል የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ኢትዮጵያ ከአሜሪካ…
Read More