Fano

የጸጥታ ሀይሎች በአማራ ክልል ሰላማዊ ዜጎችን መግደላቸው ተገለጸ

የጸጥታ ሀይሎች በአማራ ክልል ሰላማዊ ዜጎችን መግደላቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ሰላማዊ ዜጎች ከፍርድ ቤት ውጪ በአደባባዮች ላይ መገደላቸውን ኢሰመኮ ገለጸ። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ ክልል ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ መግለጫ አውጥታል። ኮሚሽኑ በሪፖርቱ በአማራ ክልል ጎንደርና ሸዋሮቢት በርካታ አካባቢዎች ከፍርድ ቤት ትዕዛዘው ውጪ ሰላማዊ ሰዎች በፀጥታ ሀይሎች መገደላቸውን የሚያመላክቱ መረጃዎች እንደደረሱት ገልጻል። ተፋላሚ ሀይሎች ያለምንም ቅደመ ሁኔታ ግጭቶችን እንዲያቆሙ፣ ለሰላማዊ ንግግር ስፍራ እንዲያመቻቹና ግጭቱ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ኮሚሽኑ አክኖም በአማራ ክልል ያለው ግጭት በሰብዓዊ መብቶች ላይ እያሳደረ ያለውን ተፅዕኖ እየተከታተለ መሆኑን ገልጾ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከመደንገጉ በፊትና በኋላ ከአዲስ አበባና ከሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መረጃዎችን እከተቀበለ እንደሆነም አስታውቋል። በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች…
Read More
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአማራ ክልል የስድስት ወራት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አጸደቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአማራ ክልል የስድስት ወራት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አጸደቀ

የተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የውሳኔ ሀሳብን በአብላጫ ድምጽ በ16 ተቃውሞ እና በ12 ድምጽ ተአቅቦ ማጽደቁ ተገልጿል። የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት በአማራ ክልል እና እንደ አስፈላጊነቱ በሌሎችም ቦታዎች ተግባራዊ ይሆናል የተባለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማጽደቁን ምክር ቤቱ በፌስቡክ ገጹ  አስታውቋል። የሚንስትሮች ምክር ቤት በአማራ ክልል በትጥቅ የተደገፈ እንቅስቃሴ መኖሩን እና ይህንንም በመደበኛው የህግ ስርአት መቆጣጠር የማይቻልበት ሁኔታ መፈጠሩን በመግለጽ ነበር ለስድስት ወራት የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የወሰነው። ምክር ቤቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቦርድ አባላትን እና ሰብሳቢዎችንም መርጧል። በአማራ ክልል፣ በፌደራል መንግስት የጸጥታ ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የተፈጠው ግጭት ንጹሃን ሰዎች እንዲገደሉ ምክንያት መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት…
Read More
አሜሪካ በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ግጭት እንዳሳሰባት ገለጸች

አሜሪካ በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ግጭት እንዳሳሰባት ገለጸች

የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር በስልክ ተወያይተዋል። ብሊንከን በዚሁ ውቅት በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል ያለው ሁኔታ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት ስጋት የሚፈጥር ነው ብለዋል። ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች የእርዳታ እህል በፍትሃዊ መንገድ በሚቀርብበት መንገድ ላይም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጋር መክረዋል። በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ያሉ ልዩነቶችንም በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት አሜሪካ ሙሉ ድጋፍ እንደምታደርግ ብሊንከን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ነግረዋቸዋል ተብሏል። በአማራ ክልል በሀገር መከላከያ እና ፋኖ መካከል ካሳለፍነው ሚያዝያ ጀምሮ ግጭት ውስጥ ገብተዋል። ግጭቱ ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን የክልሉ መንግሥት ጉዳዩ ከአቅሜ በላይ ነው ሲል የፌደራል መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ ጠይቋል። በክልል ያለው የጸጥታ ሁኔታ መባባሱን ተከትሎ የኢትዮጵያ…
Read More
በአማራ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታወጀ

በአማራ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታወጀ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፉን የጠቅላይ ሚንስቴር ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው የሕዝብን ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በቀረበው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6 /2015 ላይ ነው፡፡ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የሚታየውን በትጥቅ የተደገፈ ህገወጥ እንቅስቃሴ በመደበኛ የህግ ማስክበር ስርዓት ለመቆጣጠር ወደ ማይቻልበት ደረጃ የተሸጋገረ በመሆኑ፤ ይህ እንቅስቃሴ የክልሉን ነዋሪ አጠቃላይ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ደረጃ ያወከ እና ህገ መንግስታዊ ሥርዓቱን አደጋ ላይ የጣለ በመሆኑ፤ የሕዝብን ሠላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ እንዲሁም ህግ እና ስርዓት ለማስከበር የአስቸኳይ ጊዜ እርምጃዎችን መውሰድ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፣ እንቅስቃሴው በሃገር ደህንነት እና በህዝብ ሰላም…
Read More
በአማራ ክልል ሶስት ዞኖች ጦርነት መጀመሩ ተገለጸ

በአማራ ክልል ሶስት ዞኖች ጦርነት መጀመሩ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ ክልል የተወሰኑ አካባቢዎች እየተካሄደ ያለው “የሕግ ማስከበር ዘመቻ”ን አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል። ኮሚሽኑ ይህ ድርጊት በሰብአዊ መብቶች ላይ ያለውን አንድምታና ተጽእኖ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑ አስታውቋል። ኮሚሽኑ አደረኩት ባለው ክትትል በሰሜን ጎንደር፣ ሰሜን ወሎ እና ሰሜን ሸዋ ዞኖች አንዳንድ አካባቢዎች ግጭት አለ ብሏል። በተለይም ሸዋ ሮቢት፣ አርማኒያ፣ አንጾኪያ፣ ገምዛ እና ማጀቴ በመከላከያ ሰራዊት እና በአካባቢው ታጣቂዎች መካከል የተኩስ ልውውጥና በከባድ መሣሪያ ጭምር የታገዘ ጥቃት መኖሩን ደርሼበታለሁም ብሏል። በዚህ የተኩስ ልውውጥ ምክንያትም በሲቪል ሰዎች ላይ የሞት፣ የአካልና የንብረት ጉዳት ከመድረሱ ባለፈ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ የሚወስደው መንገድ በተለያዩ ጊዜያት መዘጋቱን እንዳረጋገጠ ኮሚሽኑ አስታውቋል። በተጨማሪም በክልሉ ያሉ የተወሰኑ…
Read More