17
Jun
ኢትዮጵያ በሩሲያ ድጋፍ እያከናወነችው የሚገኘው የባህር ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ሕንጻ ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ነው ተብሏል። ኢትዮጵያ በሩሲያ ድጋፍ በአዲስ አበባ ከተማ ጃንሜዳ አካባቢ እያከናወነችው የሚገኘው የባህር ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ሕንጻ ግንባታ 95 በመቶ መጠናቀቁ ተነግሯል። በሦስት ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የባህር ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ባለ አራት ፎቅ ሕንጻ ሲሆን፤ የአስተዳደር ቢሮዎች፣ የሕክምና ክሊኒክ፣ የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን ያካተተ ስለመሆኑ ስፑትኒክ አፍሪካ ዘግቧል። ይህም ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ቀጣናዊ ተጽዕኖ መልሳ ለማግኘት የምትከተለው ሰፊ ስትራቴጂ አካል ነው የተባለ ሲሆን፤ ፕሮጀክቱ በታቀደለት ጊዜ በቅርቡ እንደሚጠናቀቅም ተነግሯል። በተያዘው ዓመት መጋቢት ወር ላይ ኢትዮጵያ የባህር…