Ethiopianavy

ሩሲያ ለኢትዮጵያ ባህር ሀይል ድጋፍ እያደረገች መሆኑ ተገለጸ

ሩሲያ ለኢትዮጵያ ባህር ሀይል ድጋፍ እያደረገች መሆኑ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በሩሲያ ድጋፍ እያከናወነችው የሚገኘው የባህር ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ሕንጻ ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ነው ተብሏል። ኢትዮጵያ በሩሲያ ድጋፍ በአዲስ አበባ ከተማ ጃንሜዳ አካባቢ እያከናወነችው የሚገኘው የባህር ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ሕንጻ ግንባታ 95 በመቶ መጠናቀቁ ተነግሯል። በሦስት ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የባህር ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ባለ አራት ፎቅ ሕንጻ ሲሆን፤ የአስተዳደር ቢሮዎች፣ የሕክምና ክሊኒክ፣ የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን ያካተተ ስለመሆኑ ስፑትኒክ አፍሪካ ዘግቧል። ይህም ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ቀጣናዊ ተጽዕኖ መልሳ ለማግኘት የምትከተለው ሰፊ ስትራቴጂ አካል ነው የተባለ ሲሆን፤ ፕሮጀክቱ በታቀደለት ጊዜ በቅርቡ እንደሚጠናቀቅም ተነግሯል። በተያዘው ዓመት መጋቢት ወር ላይ ኢትዮጵያ የባህር…
Read More
የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ አተረፈ

የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ አተረፈ

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ በተያዘው ዓመት ውስጥ 42 ቢሊየን ብር ገቢ አግኝቻለሁ ያለ ሲሆን ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቋል። ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት ደግሞ 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን አመልክቷል። የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዋና ስራ አስፈፃሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) እንዳሉት ኮቪድ 19፣ የዩክሬንና ሩሲያ ጦርነት፣ የሀገር ውስጥ ፀጥታ ችግርና ሌሎች ችግሮች በድርጅቱ ስራዎች ላይ ተፅዕኖ ነበራቸው። በበጀት ዓመቱ ከውጭ ወደ አገር ውስጥ ከተጓጓዘው 7 ነጥብ 4 ሚሊየን ቶን እቃ ውስጥ 34 በመቶውን የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ማጓጓዙን ገልጸዋል። በመርከብ የወጪ ጭነትና ጥቅል ጭነት አገልግሎት በእቅዱ ልክ መፈፀሙን ጠቅሰው፣ በብረት ማጓጓዝ ረገድ ግን ዝቅተኛ…
Read More
ኢትዮጵያ የቀድሞ የባህር ሀይል የውጊያ ጀልባዎችን ለግዳጅ ዝግጁ አደረገች

ኢትዮጵያ የቀድሞ የባህር ሀይል የውጊያ ጀልባዎችን ለግዳጅ ዝግጁ አደረገች

ወደብ አልባ የሆነችው የኢትዮጵያ መከላከያ ዋና አዘዥ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፈጣን ተዋጊ ጀልባዎችን ጎብኝተዋል፡፡ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የአየር ኃይል አቪዬሽን ከባድ ጥገና ማዕከል ወደ አገልግሎት የመለሳቸውን ፈጣን ተዋጊ ጀልባዎችን እንደጎበኙ የሀገር መካለከያ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል። ተዋጊ ጀልባዎቹ በቀድሞ የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል አገልግሎት የሠጡ ሲሆን ዳግም የባሕር ኃይሉን ዝግጁነት ያጠናክራሉም ተብሏል። የአየር ኃይል አቪዬሽን ከባድ ጥገና ማዕከል ከ30 አመት በላይ ተገለው እና አገልግሎት መስጠት ያቆሙ ጀልባዎችን የፈጣን ተዋጊ ጀልባ ቴክኖሎጂ እና መሳሪያዎች በመግጠም ለግዳጅ ዝግጁ መደረጋቸውም ተገልጿል። ኢትዮጵያ የባህር ሀይልን እንዳዲስ በማደራጀት ላይ መሆኗን ከሁለት ዓመት በፊት መግለጿ ይታወሳል፡፡ የቀድሞ የኢትዮጵያ አካል የሆነችው ኤርትራ…
Read More