Ruleoflaw

በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጸሙት ጥቃቶች እንዲመረመሩ ለዓለማቀፉ ማሕበረሰብ ጥሪ ቀረበ

በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጸሙት ጥቃቶች እንዲመረመሩ ለዓለማቀፉ ማሕበረሰብ ጥሪ ቀረበ

አምስት ፓርቲዎች የመሰረቱት 'ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት' የተሰኘው ቅንጅት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጸሙት ጥቃቶች እንዲመረመሩ ለዓለማቀፉ ማሕበረሰብ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ቅንጅቱ በቅርቡ  በአርሲ የተፈጸመውን ግድያ አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፤“ በኢትዮጵያ የሚፈጸሙት ማንነትና ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች መንግሥታዊ መዋቅርን የተከተሉ፣ ሥርዓታዊና ተጨማሪ እጅ ያለበት ስለመኾኑ ምርመራ እንዲደረግ ” ጥሪውን አቅርቧል። ቅንጅቱ፤ “ጠያቂም ተጠያቂም ባለመኖሩ መግደል ቀላል ኾኗል” በሚል  ያወጣው መግለጫ፤ “ እንዲህ ዓይነቱን ግዙፍ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት" በጽኑ እንደሚያወግዝ አስታውቆ፣ "እልቂት የየቀን ገጠመኙ ለኾነው የአካባቢው ማኅበረሰብም" ብርታትና መጽናናትን ተመኝቷል። መላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድነት ፓርቲ (ኢሕአፓ)፣ እናት ፓርቲ፣ አዲሲ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አኢዴፓ) እና አማራ ግዮን ንቅናቄ ( አግን) የመሠረቱት ' ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት…
Read More
በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ህግ በጣሱ ፖሊሶች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ህግ በጣሱ ፖሊሶች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ህግ በጣሱ የፖሊስ አባላት ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ። በዘንድሮው የአድዋ በኣል በአዲስ አበባ ምኒልክ አደባባይ የጸጥታ ሀይሎች በዜጎች ላይ ያልተገባ ድርጊት መፈጸማቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ እና ሌሎችም ተቋማት መናገራቸው ይታቀሳል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በጉዳዪ ዙሪያ ዛሬ በሰጠው መግለጫ በዕለቱ የህግ ጥሰት በፈጸሙ የፖሊስ አባላት ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል። ኮሚሽኑ አክሎም በዓሉ በተከበረበት እለት የከተማዋን ሰላም አውከዋል በሚል 878 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር አውያለሁ ብሏል። በህግ ቁጥጥር ስር ከዋሉት ውስጥም 557ቱ ከሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ መሆናቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን…
Read More