13
Aug
ኢትዮጵያ በፕሬዚዳንት እንድትመራ በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ተመካካሪዎች መግባባት መደረሳቸው ተሰምቷል። ይሁንና ፕሬዚዳንቱ በሕዝብ ይመረጥ ወይስ በፓርላማ በሚለው ጉዳይ ተመካካሪዎች ስምምነት ላይ አለመድረሳቸው ተገልጿል። ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ቀርቶ በፕሬዚዳንት እንድትመራ፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ እንዲሁም የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልናና የምርጫ ሥርዓት አጀንዳ ላይ የ500 ቡድን ተመካካሪዎች ሙሉ በሙሉ በምክረ-ሐሳብ ደረጃ መግባባት ላይ ደርሰዋል ተብሏል። በዚሁ አጀንዳ ላይ ተወያይ የነበሩ ተመካካሪዎች ለሪፖርተር በሰጡት አስተያየት፣ በቀረቡት አብዛኞቹ ምክረሐሳቦች መግባባት ላይ መደረሱን ሆኖም ያላግባቡና ወደ ቀጣይ የተሻገሩ ጉዳዮች መኖራቸውንም ገልጸዋል። በዚህም የ500 ቡድን ተመካካሪዎች የአገሪቱ አስተዳደር ሥርዓት ፓርላሜንታሪ ሆኖ እንዲቀጥል፣ የአገሪቱ መሪ ፕሬዚዳንት እንዲሆን፣ አዲሱ ተመራጭ ፕሬዚዳንትም የጠቅላይ ሚኒስትሩና የፕሬዚዳንቱ ሥልጣንና ተግባርን…