Ethiopiamaritime

ኢትዮጵያ የ6 መርከቦች ግዥ መፈፅሟ ተገለ

ኢትዮጵያ የ6 መርከቦች ግዥ መፈፅሟ ተገለ

የመርከቦቹ መገዛት በባህር ትራንስፖርት ላይ ያላትን አቅም የበለጠ ያሳድጋል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የሚያስተዳድራቸው 10 መርከቦች ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ የማዳበሪያ ምርትን ጨምሮ የሚበዛውን ምርት የምታጓጉዘው እነዚህኑ መርከቦች ተጠቅማ ነው። አሁን ደግሞ የተጨማሪ ስድስት ትላልቅ መርከቦች ግዢ ተፈፅሞ ኢትዮጵያ መርከቦቹን ዘንድሮ እንደምትረከብ ተነግሯል። ይህም ኢትዮጵያ በውሃ ትራንስፖርት ላይ ያላትን አቅም የሚያሳድግ ነው ተብሏል። ከስድስቱ መርከቦች ሁለቱ እስከ 62,000 ቶን የመጫን አቅም ያላቸው እንደሆኑም ተነግሯል። ኢትዮጵያ አሁን ካሏት አስር መርከቦች አባይ ሁለት በመባል የምትጠራው እስከ 63,000 ቶን የመጫን አቅም እንዳላት ይነገራል። ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያ ወደ ሀገር ውስጥ ካስገባችው 1.9 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን የማዳበሪያ ምርት አብዛኛው ተጓጉዞ ጅቡቲ ወደብ የደረሰው በራሷ መርከቦች…
Read More
ኢትዮጵያ ስድስት የጭነት መርከቦችን ልትገዛ ነው ተባለ

ኢትዮጵያ ስድስት የጭነት መርከቦችን ልትገዛ ነው ተባለ

የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ስድስት አዳዲስ የጭነት መርከቦችን ግዢ ሊፈፀም እንደሆነ አስታውቋል። 62 ሺህ ቶን የመጫን አቅም ያላቸው ሁለት አልትራማክስ የደረቅ ብትን ጭነት መርከቦች በአጭር ግዜ ተገዝተው አገልግሎት እንደሚጀምሩ ድርጅቱ ገልጿል፡፡ የቀሪ አራት መርከቦች ግዥ በቀጣዮቹ ዓመታት እንደሚፈፀም የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስን ጠቅሰው የሀገር ውስጥ ሚዲያዎች ዘግበዋል። ኢትዮጵያ መርከቦቹን የምትገዛው የሀገሪቱን የገቢ ወጪ ንግድ እንቅስቃሴ ያግዛሉ በሚል ነው፡፡ ኢትዮጵያ አሁን ላይ 10 መርከቦች እንዳሏት ይነገራል። ከሁለት ዓመት በፊት ኢትዮጵያ ከ60 ሺህ ቶን በላይ እቃ የመጫን አቅም ያላትን መርከብ መረከቧ ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ በቅርቡ ባህር ዳር እና ሀዋሳ የተሰኙ ሁለት መርከቦች ለኪሳራ ዳርገውኛል በሚል መሸጡ ይታወሳል። በተሸጡት ሁለት መርከቦች…
Read More
የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ አተረፈ

የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ አተረፈ

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ በተያዘው ዓመት ውስጥ 42 ቢሊየን ብር ገቢ አግኝቻለሁ ያለ ሲሆን ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቋል። ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት ደግሞ 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን አመልክቷል። የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዋና ስራ አስፈፃሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) እንዳሉት ኮቪድ 19፣ የዩክሬንና ሩሲያ ጦርነት፣ የሀገር ውስጥ ፀጥታ ችግርና ሌሎች ችግሮች በድርጅቱ ስራዎች ላይ ተፅዕኖ ነበራቸው። በበጀት ዓመቱ ከውጭ ወደ አገር ውስጥ ከተጓጓዘው 7 ነጥብ 4 ሚሊየን ቶን እቃ ውስጥ 34 በመቶውን የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ማጓጓዙን ገልጸዋል። በመርከብ የወጪ ጭነትና ጥቅል ጭነት አገልግሎት በእቅዱ ልክ መፈፀሙን ጠቅሰው፣ በብረት ማጓጓዝ ረገድ ግን ዝቅተኛ…
Read More
ኢትዮጵያ ከ60 ሺህ ቶን በላይ እቃ የመጫን አቅም ያላትን መርከብ ተረከበች

ኢትዮጵያ ከ60 ሺህ ቶን በላይ እቃ የመጫን አቅም ያላትን መርከብ ተረከበች

ኢትዮጵያ ከ60 ሺህ ቶን በላይ እቃ የመጫን አቅም ያላትን መርከብ ተረከበች የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ በቅርቡ ባህር ዳር እና ሀዋሳ የተሰኙ ሁለት መርከቦች ለኪሳራ ዳርገውኛል በሚል መሸጡ ይታወሳል። በተሸጡት ሁለት መርከቦች ምትክም አባይ የተሰኘች አዲስ መርከብ ከቻይና መግዛቱን አስታውቋል። አዲሷ መርከብም በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት ታሪክ በግዙፍነቷ አቻ የላትም የተባለ ሲሆን መርከቧ በኢትዮጵያ እጅ መግባቷን ድርጅቱ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ድርጅት በ3 ሺህ ቶን የመጫን አቅም ባላቸው መርከቦች ስራውን መጀመሩ ይታወሳል። ኢትዮጵያ የተረከበቻት አባይ የተሰኘችው አዲሷ መርከብ 63 ሺህ 229 ቶን የመጫን አቅም አላት ተብሏል። በቻይናው ያንግዡ ዳያንግ ሺፕ ቢዩልዲንግ የተገነባችው ይህች መርከብ 200 ሜትር ርዝመት እንዳላትም ተገልጿል። ይሁንና…
Read More