Amharabank

ዶክተር ዮሀንስ አያሌው የጸደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ

ዶክተር ዮሀንስ አያሌው የጸደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ

የቀድሞው ልማት ባንክ እና አማራ ባንክ ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሀንስ አያሌው በኪሳራ ላይ ላለው ጸደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ተደርገው ተሾመዋል። የአማራ ብድርና ቁጠባ ድርጅት በሚል ሲጠራ የነበረው በኋላም ጸደይ ባንክ በሚል ስያሜ የኢትዮጵያን የባንክ ቢዝነስ የተቀላቀለው ጸደይ ባንክ በኪሳራ ላይ ይገኛል። ባንኩ በ2024/25 በጀት ዓመት ብቻ የሁለት ቢሊዮን ብር ኪሳራ እንደደረሰበት ከአንድ ወር በፊት ዓመታዊ ጉባኤውን ሲያካሂድ ገልጿል። ይህን ተከትሎም ዶክተር ዮሀንስ አያሌው የባንኩ አዲስ ፕሬዝዳንት ሆነው እንደተሾሙለት ባንኩ ከደቂቃዎች በፊት በማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ አስታውቋል። በኪሳራ ላይ ያሉ የገንዘብ ድርጅቶችን በመታደግ የሚታወቁት ዶክተር ዮሀንስ ከዚህ በፊት ልማት ባንክን እንዲሁም የአማራ ባንክን ከኪሳራ ወደ ትርፍ መመለሳቸው ይገለጿል። ላለፉት ዓመታት ጸደይ ባንክን በፕሬዝዳንትነት…
Read More
ዮሀንስ አያሌው(ዶ/ር) የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ

ዮሀንስ አያሌው(ዶ/ር) የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ

ባለፈው ሳምንት ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ በጤና እክል ምክንያት ከሃላፊነት የለቀቁት ዮሀንስ አያሌው ብሩ (ዶ/ር)፣ የአማራ ባንክ አክሲዮን ማኅበር የዳይሬክተሮች ቦርድ  ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሸመዋል፡፡ የአማራ ባንክ በማህበራዊ ትስስር ገጾቹ ላይ እንዳጋራው ዩሀንስ አያሌው ከዛሬ መስከረም 3 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በዋና ስራ አስፈጻሚነት መሾማቸውን ገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ የግል ባንኮች ታሪክ በሰባት ቢሊዮን ብር መነሻ ካፒታል ከሁለት ዓመት በፊት ስራ የጀመረው የአማራ ባንክ 138 ሺህ ባለ አክስዮኖች የመሰረቱት የግል ባንክም ነው፡፡ ዮሐንስ አያሌው በልማት ባንክ የስራ ዘመናቸው ባንኩ ከነበረበት ውስብስብ ችግርና ክስረት  ወደ ተሻለ አቋም እንዲመለስ ማስቻላቸው ይታወሳል። በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ጠለቅ ያለ እውቀት እንዳላቸው የሚነገርላቸው ዶክተር ዮሀንስ አያሌው ከዚህ ቀደም…
Read More
አማራ ባንክ ፕሬዝዳንቱን ከሀላፊነት አነሳ

አማራ ባንክ ፕሬዝዳንቱን ከሀላፊነት አነሳ

የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኄኖክ ከበደ ከሓላፊነታቸው ተነሱ የአማራ ባንክ የዲሬክተሮች ቦርድ ፕሬዝዳንቱ አቶ ሔኖክ ከበደ ባንኩን ለ460 ሚሊዮን ብር ኪሳራ ዳርገዋል በሚል ከሀላፊነት አንስቷል፡፡ ባንኩ ከዋና ሥራ አስፈጻሚው በተጨማሪም የኮርፖሬት አገልግሎት ዋና መኰንኑን አቶ ክንዴ አበበን፣ የአፈጻጸም ድክመት አሳይተዋል በሚል በባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር  መላኩ ፈንታ ፊርማ ከሓላፊነታቸው አንሥቷል። የባንኩ ቦርድ ውሳኔውን ያሳለፈው፣ ኹለቱም ከፍተኛ ሓላፊዎች፣ ከተሾሙበት ዕለት ጀምሮ፣ በየጊዜው በሚሳዩት የሥራ አፈጻጸም ድክመት፣ የባንኩን ስትራቴጂያዊ ግቦች እና ቁልፍ የአፈጻጸም መመዘኛዎችን ማሳካት አልቻሉም ተብሏል፡፡ ባንኩ በ2014/15 ዓ.ም. ከ306 ሚሊዮን ብር በላይ ትርፍ ለማስመዝገብ ዐቅዶ የነበረ ቢኾንም፣ ብር 460,286,000 ኪሳራ አስመዝግቧል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ በሌላቸው ሥልጣን ባሳለፉት አስተዳደራዊ…
Read More