04
Sep
በርካታ መጠን ያላቸው የውጭ ሀገራት ገንዘቦችን በማተምና ጥቁር ገበያን በማስፋፋት ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ። ተጠርጣሪዎቹ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል። በኢትዮጵያ መዲና አዲስ አበባ ቻይናዊያን ባለሀብቶች ንብረት የሆነው ፀሃይ ሪል ስቴት በዚህ ወንጀል እጁ እንዳለበት ፖሊስ ገልጿል። ፖሊስ የሪል ኢስቴቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ኪያ ዦንግን ጨምሮ ዘጠኝ የውጭ ሀገራት ዜጎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል። ፖሊስ በህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ካዋላቸው የውጭ ሀገራት ዜጎች ውስጥ ሶስት ኢትዮጵውያን ተጠርጣሪዎችም ተይዘዋል። ፖሊስ ሁሉንም ተጠርጣሪዎችን ፍርድ ቤት አቅርቦ ተጨማሪ ምርመራዎችን ለማድረግ የ14 ቀናት ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል። ፖሊስ…