21
Aug
10 የስራ ተቋራጭ ድርጅቶች ከኢትዮጵያ ውጪ ውጪ ባሉ ሀገራት መሰማራታቸውን የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚንስቴር አስታውቋል ሚንስቴሩ በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የተሰማሩ የኢትዮጵያ ስራ ተቋራጭ ድርጅቶችን ቁጥር 20 የማድረስ እቅድ መያዙን ገልጿል። የሀገራቱን አስፈላጊ መስፈርት አሟልተውና በጨረታ አሸንፈው በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ በኮንስትራክሽን ሥራዎች ላይ የሚሳተፉ ተቋራጮችን ቁጥር ወደ 20 ከፍ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር አስታውቋል። የሚንስትሩ ሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኢትዮጵያ በዴቻ፤ "ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የግንባታ ሥራ ለማከናወን ፈቃድ ተሰጥቷቸው በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የኮንትራት ሥራዎችን ወስደው በግንባታ ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የግንባታ ስራ ተቋራጮች ቁጥር ከ10 አይበልጥም" ብለዋል፡፡ በመሆኑም ሚኒስቴሩ ይህን የግንባታ ሥራ ተቋራጮች…