AUSummit2024

የአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

የአፍሪካ ህብረት ዓመታዊ የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል። ስብሰባው “ የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ዘርዓ አፍሪካውያን” በሚል የአፍሪካ ሕብረት ባዘጋጀው የ2025 መሪ ሃሳብ የሚካሄድ ነው። በስብሰባው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማህማት፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ የሀገራት መሪዎች እና ሌሎች ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል። ከዛሬ ጀምሮ ለሁት ቀናት የሚመክረው የመሪዎች ጉባዔ ከሁለት ቀናት በፊት በተጠናቀቀው 46ኛው የሕብረቱ የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት በመደበኛ ስብሰባ በተለዩ አጀንዳዎች ላይ ይመክራል። ከዘንድሮው የመሪዎች ጉባዔ አጀንዳዎች መካከል የሕብረቱ ተቋማዊ ማሻሻያዎች፣ የማካካሻ…
Read More
የአፍሪካ ህብረት ሳይጋበዙ ጉባኤውን ለመሳተፍ የሚመጡ ሰዎችን አስጠነቀቀ

የአፍሪካ ህብረት ሳይጋበዙ ጉባኤውን ለመሳተፍ የሚመጡ ሰዎችን አስጠነቀቀ

የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች የሚሳተፉበት 44ኛው የአፍሪካ ህብረት ስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው። የህብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ደግሞ የፊታችን ቅዳሜ እና እሁድ የሚካሄድ ሲሆን በዚህ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ለሚመጡ ታዛቢ ሀገራት ማስጠንቀቂያ አውጥቷል፡፡ ህብረቱ ባወጣው መግለጫ በታዛቢነት እንዲሳተፉ ከተጋበዙ ሀገራት እና ተቋማት ውጪ የሚመጡ ተሳታፊዎችን እንደማያስተናግድ አስጠንቅቋል፡፡ 37ኛው የህብረቱ መሪዎች እና 44ኛው የህብረቱ ስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ጉባኤን በታዛቢነት እንዲሳተፉ ከተፈቀደላቸው ሀገራት እና ተቋማት ውጪ እንዳይመጡ እና ፈቃድ የተሰጣቸው ደግሞ ከአንድ ተወካይ በላይ እንዳይመጡ ሲልም ህብረቱ አሳስቧል፡፡ ከዚህ በፊት በአፍሪካ ህብረት ጉባኤዎች ላይ በታዛቢነት እንዲሳተፉ ፈቃድ የተሰጣቸው ሀገራት እና ተቋማትም ፈቃዳቸውን እንዲያድሱ ሲልም…
Read More