Livertransplant

በአዲስ አበባ የጉበት ንቅለ ተከላ ህክምና ማዕከል ሊማቋቋም ነው

በአዲስ አበባ የጉበት ንቅለ ተከላ ህክምና ማዕከል ሊማቋቋም ነው

በኢትዮጵያ የጉበት ንቅለ ተከላ ፕሮግራም በትብብር ለማቋቋም የሚያስችል ስምምነት በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ፣ በጤና ሚኒስቴር እና በካሊፎርኒያ ፓሲፊክ የሕክምና ማዕከል መካከል ተፈርሟል። ይህ ተነሳሽነት በትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ዶ/ር ቅድስት ኪዳኔ ይማም የሚመራ ሲሆን በሰሜን ካሊፎርኒያ ያሉ ባልደረቦቻቸውን በማስተባበር ወደ ተግባር የተቀየረ ነው። ከዚህ ቀደም ዶ/ር ቅድስት አገልግሎቱን በቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ሆስፒታል የጉበት ንቅለ ተከላ ጨምሮ የተለያዩ አገልግሎቶች ለመስጠት የሚያስችል የህክምና ክፍል ለመመስረት የሙያ ስልጠናዎች እና የቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ ቆይተዋል። ኢትዮጵያ ሄፐታይተስ ቢ እና ሄፐታይተስ ሲ በተሰኙት የጉበት በሽታ ተጠቂዎች ከፍተኛ ከሆነባቸው የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን የዓለም ጤና ድርጅት ከሶት ወራት በፊት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ በቅዱስ ጳውሎስ…
Read More