08
Apr
ኢትዮጲያ ውስጥ ሴቶች እና ልጃገረዶች ከማህበራዊ ኑሮ እየተገለሉ እና በማህበራዊ ትሥሥር ድረ-ገፆች ላይም በተደጋጋሚ መገፋት እና ማጥላላት እየደረሰባቸዉ ነዉ። እነዚህ ግኝቶች ሴንተር ፎር ኢንፎርሜሽን ሪዚሊየንስ (ሲ.አይ.አር) በተባለ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን፣ የሀሰት መረጃን እና ኢንተርኔት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን መከላከል ላይ አተኩሮ በሚሰራ ገለልተኛና ለትርፍ ባልተቋቋመ ተቋም በተደረጉ ጥናቶች የተገኙ ናቸው። ይህ ጥናት ሲ.አይ.አር ኢትዮጲያ ውስጥ በፌስቡክ፣ ኤክስ (X) እና ቴሌግራም ላይ የሚፈጸሙ ጾታን መሰረት ያደረጉ ትንኮሳዎች ላይ ቀደም ብሎ ያደረገውን ጥናት ወደ ሁለት ተጫማሪ የማህበራዊ ትሥሥር ድረ-ገፆች ማለትም ዩትዩብና ቲክቶክ አስፋፍቷል። ግኝቶቹም እንደሚያሳዩት በማህበራዊ ትሥሥር ድረገፆች ላይ የሚደረጉ የጥላቻ ንግግሮች የሰዎችን የመናገር፣ የመምራት እና በዲጂታሉ አለም ያላቸውን ደህንነት እየገደበ እንዳለና እና…