Localflight

የክልል አየር ማረፊያዎች ዓለም አቀፍ በረራዎች ማስተናገድ ሊጀምሩ ነው

የክልል አየር ማረፊያዎች ዓለም አቀፍ በረራዎች ማስተናገድ ሊጀምሩ ነው

ዓለም አቀፍ በረራዎችን ከአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በተጨማሪ በሌሎች የክልል አየር ማረፊያዎች ማስተናገድ ሊጀመር መሆኑን የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታውቋል። ባለስልጣኑ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዶ/ር አለሙ ስሜ፣ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሃንስ አበራ፣ ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች እና የግል አየር ትራንስፖርት ኦፕሬተር ተወካዮች በተገኙበት፤ የአየር ትራንስፖርት ዘርፍ የባለድሻ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ አካሂዷል። በባለስልጣኑ የአየር ትራንስፖርትና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች አማካሪ አቶ እንደሻው ይገዙ ባቀረቡት ሪፖርት፤ በ2018 ዓ.ም ዓለም አቀፍ በረራዎችን ከአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በተጨማሪ በሌሎች የሀገሪቱ ክልል ኤርፖርቶች ማስተናገድ እንደሚጀመር ተናግረዋል። "የክልል ኤርፖርቶችን ማስተሳሰር የቱሪዝም ፍሰቱ እንዲጨምር እንዲሁም የደንበኛውን እንግልት መቀነስ የሚያስችል ነው" ያሉት አቶ…
Read More