03
Dec
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት በገንዘብ ችግር ምክንያት ለመዘጋት የተቃረቡ መደበኛ መገናኛ ብዙኃንን ለመታደግ እና የነፃ ሚዲያ ድምፅ እንዳይቋረጥ የሚያግዝ የመገናኛ ብዙኃን የገንዘብ ድጋፍ ቋት (የሚዲያ ፈንድ) ለማቋቋም የሚያስችል ውይይት ማካሄዱን አስታውቋል። "የሚቋቋመው ፈንድ ለግልና ለሕዝብ የሚዲያ ተቋማት የገንዘብ ድጋፍ ያደርጋል" የተባለ ሲሆን፤ በተለያየ ምክንያት ከሥራ ውጪ በመሆናቸው ገቢያቸው የተቋረጠ ጋዜጠኞችን መታደግ ላይ እንደሚሰራም ተገልጿል። የምክር ቤቱ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ታምራት ኃይሉ ባቀረቡት ጥናት፤ በርካታ የሚዲያ ተቋማት በአሁኑ ወቅት በሕትመት ወጪ መናር፣ በሳተላይት ክፍያ ውድነት እንዲሁም በሠራተኞች ደመወዝና የአስተዳደር ወጪ መናር ምክንያት ህልውናቸው አደጋ ውስጥ መግባቱን አብራርተዋል። አቶ ታምራት እንደገለጹት፤ በሰለጠኑት ሀገራት የአንድ ሚዲያ መዘጋት እንደ አንድ…