ኢትዮጵያ እና ኬንያ ወታደራዊ ስምምነት ተፈራረሙ

ኢትዮጵያ እና ኬንያ ከ62 ዓመታት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ታሪካዊ የሚባል ወታደራዊ ስምምነት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱ ከሁለቱ ሀገራት ባለፈ ለቀጠናው ሰላምና መረጋጋትም የጎላ ፋይዳ ያለው መሆኑም ተገልጿል።

ስምምነቱን የኢትዮጵያ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና የኬንያ መከላከያ ኢታማዦር ሹም ጄነራል ቻርልስ ሙሪዩ ካሃሪሪ ፈርመዋል።

ስምምነቱ ከሃገራቱ በተጨማሪ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የጎላ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ እና የኬንያ መከላከያ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ቻርልስ ሙሪዩ ካሃሪሪ ተናግረዋል።

በቀጣይም ከኢትዮጵያ መከላከያ ጋር በትብብር በሚሰሩ ስራዎች ዙሪያ የኬንያ መከላከያ በቁርጠኝነት ለመስራት ፍላጎት ያለው መሆኑን ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ቻርልስ ሙሪዩ ካሃሪሪ መናገራቸውንም ከኢኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ኢትዮጵያና ኬንያ ከዚህ በፊት ወታደራዊ ስምምነት የተፈራረሙት በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ታኅሳስ 1963 ኬንያ ነፃነቷን በተቀዳጀችበት ዓመት ላይ እንደነበር ይታወሳል።

ኢትዮጵያ እና ኬንያ ከዚህ በፊት ሽብርተኝነት በጋር ለመከላከል የሚያስችል ስምምነት ያላቸው ሲሆን ስምምነቱ ታጣቂዎችን አለማስጠለልን ይጨምራል።

በኦሮሚያ ክልል በስፋት የሚንቀሳቀሰው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት በሁለቱ ሀገራት ድንበር አካባቢዎች ላይ በስፋት እንደሚንቀሳቀስ ይጠቀሳል።

የአሁኑ ስምምነት የኦነግ ሰራዊትን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር እንደሚረዳ ይጠበቃል።

ኢትዮጵያ እና ኬንያ በጋራ የሚሰሩባቸውን ጉዳዮች ቀስ በቀ እያሰፉ የመጡ ሲሆን ንግድ፣ ኢንቨስትመንት ፣ የሀይል ትስስር እና ወታደራዊ ትብብሮች ዋነኞቹ ናቸው።

ይህ በዚህ እንዳለ ግብፅ የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ የኢትዮጵያ ግድብ ምረቃ ላይ በመገኘታቸው መበሳጨቷ ተሰምቷል።

በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃ ላይ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ከተገኙ በኋላ ዝግጅቱ በናይል ተፋሰስ ውሃ ላይ እየተካሄደ ያለውን ድርድር የሚያበላሽ ነው በማለት ስጋቷን በመጥቀስ ግብፅ ብስጭቷን ገልጻለች።

በኬንያ የግብፅ ተወካይ አምባሳደር ሃተም ዩስሪ ሆስኒ ረቡዕ September 24/2015 የግድቡ ግንባታ አለም አቀፍ ህግጋትን የሚጻረር እና የተደረሰውን የህግ ማዕቀፎችን የማያከብር ነው ብለዋል።

ግብፅ እያንዳንዱ የናይል ተፋሰስ ሀገራት በኤሌክትሪክ ኃይል ከውሃው ተጠቃሚ የመሆን መብታቸውን እንደምታከብር ገልፀው፣ በምስረታው ላይ ኬንያ በመሳተፏ ቅር እንዳሰኛቸው ገልጸዋል።

“በዚያ ዝግጅት ላይ ኬንያ መወከሏ በጣም አበሳጭቶናል፤ ከናይል ተፋሰስ ሀገራት ውስጥ ሀገር ኬንያ ብቻ ነች የተገኘችው፤ ጅቡቲ እና ሶማሊያ የናይል ተፋሰስ አካል አይደሉም” ብሏል።

By New admin

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *