DrLiaTadesse

ኢትዮጵያ ለቤተሰብ እቅድ አገልግሎት የ36 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አገኘች

ኢትዮጵያ ለቤተሰብ እቅድ አገልግሎት የ36 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አገኘች

በጀቱ የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል እንደሆነ ተገልጿል። የ36 ሚሊዮን በጀት ስምምነቱ በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት በኢትዮጵያ የቤተሰብ ዕቅድን ተደራሽ ለማድረግ ይውላል ተብላል። በኢትዮጵያ 22 በመቶ ሴቶች የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ተደራሽ ያልሆነላቸው ሲሆን በጀቱ ከዚህ አንጻር ተጨማሪ ሴቶችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገልጿል። በበጀት ስምምነቱ ላይ የተገኙት የጤና ጥበቃ ሚንስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳሉት የቤተሰብ እቅድ አገልግሎቱን ተደራሽነት ለማጠናከር እንቅፋት ከሆኑ ችግሮች መካከል አገልግሎቱ በነፃ የሚሰጥና ወጭው በአብዛኛው  በለጋሽ አካላት የሚሸፈን በመሆኑና ከለጋሽ አካላት የሚገኘው ድጋፍ እየቀነሰ መምጣቱ ነው ብለዋል። እንዲሁም በአለም አቀፍ ደረጃ የዋጋ ንረት በመኖሩ ለግብዓት የሚያስፈልግ የበጀት ዕጥረት ማጋጠሙን የጠቆሙት ሚንስትሯ ችግሩን በመቅረፍ አቅርቦቱን እንዳይቆራረጥ ለማድረግ  በመደበኛነት ከሚመደበው በጀት…
Read More