የኢትዮጵያ አየር መንገድ 100 ሚሊዮን መንገደኖችን የሚያስተናገድ ኤርፖርት ሊያስገነባ መሆኑን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ አውሮፕላን ጣቢያ ለመገንባት በሂደት ላይ መሆኑን አስታውቋል።

በዓመት 100 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው አውሮፕላን ጣቢያ በቢሾፍቱ ከተማ እንደሚገነባ ገልጿል።

ይህ አውሮፕላን ጣቢያ ወይም ኤርፖርት የሚገነባው በዓመት 25 ሚሊዮን መንገደኞችን ብቻ የማስተናገድ ያለው ቦሌ ዓከም አቀፍ ኤርፖርትን ለመተካት እንደሆነ የተቋሙ ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ተናግረዋል።

በቢሾፍቱ ልዩ ስሙ አቡ ሴራ በተባለው ስፍራ የሚገነባው ይህ ኤርፖርት ግንባታ ዲዛይን ዳር የተሰኘው ኩባንያ መመረጡንም አቶ መስፍን ገልጸዋል።

አቶ መስፍን አክለውም አዲሱ ኤርፖርት ግንባታ በአምስት ዓመታት ውስጥ በሁለት ዙር ይገነባል ያሉ ሲሆን ለመጀመሪያው ዙር ግንባታ ስድስት ቢሊዮን ዶላር ወጪ ይደርግበታልም ብለዋል።

ኤርፖርቱ ባንድ ጊዜ አራት አውሮፕላኖችን የማሳረፍ እና መንደርደሪያ መም ይኖረዋል ተብሏል።

270 አውሮፕላኖችን የማሳረፍ አቅም ያለው አዲሱ ኤርፖርት ከቦሌ ኤርፖርት ጋር የሚያስተሳስር ፈጣን ባቡር እና መንገድ እንደሚገነባ ተገልጿል።

ለአዲሱ ኤርፖርት ግንባታ የሚያስፈልገው ስድስት ቢሊዮን ዶላር ወጪ በብድር እንደሚሸፈን የተገለጸ ሲሆን ብድር ለመስጠት የሚፈልጉ ተቋማት መገኘታቸውንም አቶ መስፍን ተናግረዋል።

ይሁንና የአዲሱን ኤርፖርት ግንባታ ዲዛይን የሚሰራው ዳር ኩባንያ ወጪ ምን ያህል እንደሆነ አቶ መስፍን ከማገር ተቆጥበዋል።

By New admin

One thought on “የኢትዮጵያ አየር መንገድ 100 ሚሊዮን መንገደኖችን የሚያስተናገድ ኤርፖርት ሊያስገነባ መሆኑን ገለጸ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *