27
Feb
ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ ለዘንድሮ የዓድዋ ድል በዓል መታሰቢያ ለቦረና ወገኖች አስቸኳይ ድጋፍ የሚውል 1,000,000.00 (አንድ ሚልየን) ብር ለግሷል። በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ከ800 ሺህ በላይ ዜጎች በድርቅ መጎዳታቸው ሲታወስ ከ3 ሚሊዮን በላይ የቤት እንስሳትም ሞተዋል፡፡ ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን ቴዲ አፍሮ የዘንድሮን የዓድዋ ድል በዓል መታሰቢያ ምክንያት በማድረግ በድርቅ ሳቢያ አስቸኳይ እርዳታ ለሚፈልገው የቦረና ሕዝባችን የ1ሚልየን ብር ድጋፍ አድርጓል። በቦረና ዞን ለተከታታይ ለስድስተኛ ጊዜ ዝና ብ አለመዝነቡን ተከትሎ በድርቁ የተጎዱ ሰዎች ቁጥር መጨመሩን የዞኑ አስተዳድር አስታውቋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር 100 ሚሊዮን ብር በቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ሰዎች ድጋፍ ሲያደርግ ሌሎችም የመንግስት እና የግል ተቋማትም ድጋፍ ማድረጋቸውን ቀጥለዋል፡፡ በኢትዮጵያ…