01
Mar
የሩስያ መከላከያ ሚኒስቴር በሰሜናዊ ክሬሚያ በሚገኝ ወታደራዊ መጋዘን የደረሰውን ፍንዳታ ተከትሎ ከ3,000 በላይ ሰዎችን አካባቢዉን ለቀው እንዲወጡ ያስገደደ ሲሆን የሴራ ዉጤት ነዉ ሲል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ማስታወቁን የሩሲያ መንግስት ሚዲያ ዘግቧል። በትላንትናዉ እለት የደረሱት ፍንዳታዎች በሜይስኮዬ መንደር አቅራቢያ በሚገኘው የጥይት ማከማቻ ቦታን ያናወጡ እና የባቡር አገልግሎቶችን እንዲሁም የሃይል አቅርቦቶችን ያስተጓጎለ ነበር፡፡ በፍንዳታው በሰው ላይ ከባድ ጉዳት እንዳልደረሰ ሚኒስቴሩ አክሏል።የሩሲያ ኮምመርሰንት ጋዜጣ በትላንትናዉ እትሙ በክሬሚያ ተጨማሪ ጥቃት ሊፈጸም እንደሚችል ዘግቧል፡ እማኞችን ጠቅሶ እንደዘገበው በግቫርዴስኮዬ ባሕረ ገብ መሬት ላይ በሚገኘው የሩሲያ ወታደራዊ አየር ማረፊያ ላይ ጭስ መታየቱን ጽፏል፡፡ባለፈው ሳምንት በክሬሚያ በሩሲያ ስር በሚተዳደረው የአየር ጣቢያ ላይ የደረሰ ፍንዳታ የነበረ ሲሆን ሞስኮ በወቅቱ…