New admin

1105 Posts
ሩሲያ በክሬሚያ የጦር መሳሪያ ማከማቻ ስፍራ ላይ የደረሰዉ ፍንዳታ በሴራ ነዉ ስትል ተናገረች

ሩሲያ በክሬሚያ የጦር መሳሪያ ማከማቻ ስፍራ ላይ የደረሰዉ ፍንዳታ በሴራ ነዉ ስትል ተናገረች

የሩስያ መከላከያ ሚኒስቴር በሰሜናዊ ክሬሚያ በሚገኝ ወታደራዊ መጋዘን የደረሰውን ፍንዳታ ተከትሎ ከ3,000 በላይ ሰዎችን አካባቢዉን ለቀው እንዲወጡ ያስገደደ ሲሆን የሴራ ዉጤት ነዉ ሲል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ማስታወቁን የሩሲያ መንግስት ሚዲያ ዘግቧል። በትላንትናዉ እለት የደረሱት ፍንዳታዎች በሜይስኮዬ መንደር አቅራቢያ በሚገኘው የጥይት ማከማቻ ቦታን ያናወጡ እና የባቡር አገልግሎቶችን እንዲሁም የሃይል አቅርቦቶችን ያስተጓጎለ ነበር፡፡ በፍንዳታው በሰው ላይ ከባድ ጉዳት እንዳልደረሰ ሚኒስቴሩ አክሏል።የሩሲያ ኮምመርሰንት ጋዜጣ በትላንትናዉ እትሙ በክሬሚያ ተጨማሪ ጥቃት ሊፈጸም እንደሚችል ዘግቧል፡ እማኞችን ጠቅሶ እንደዘገበው በግቫርዴስኮዬ ባሕረ ገብ መሬት ላይ በሚገኘው የሩሲያ ወታደራዊ አየር ማረፊያ ላይ ጭስ መታየቱን ጽፏል፡፡ባለፈው ሳምንት በክሬሚያ በሩሲያ ስር በሚተዳደረው የአየር ጣቢያ ላይ የደረሰ ፍንዳታ የነበረ ሲሆን ሞስኮ በወቅቱ…
Read More
የሮበርት ሙጋቤ ልጅ ድግስ ላይ ንብረት አውድሟል ተብሎ ታሠረ

የሮበርት ሙጋቤ ልጅ ድግስ ላይ ንብረት አውድሟል ተብሎ ታሠረ

የቀድሞው የዚምባብዌ ፕሬዝደንት ሮበርት ሙጋቤ ወንድ ልጅ ሃራሬ ውስጥ በተዘጋጀ ድግስ ላይ ንብረት አውድሟል ተብሎ በቁጥጥር ሥር ዋለ። 31 ዓመቱ እንደሆነ የሚገመተው ሮበርት ሙጋቤ ጁኒዬር ሶስት ንብረት የማውደም እና ሁለት ፖሊስ የመተናኮስ ክስ ቀርቦበታል ሲሉ ጠበቃቸው ተናግረዋል። በድግሱ ላይ የመኪናዎች መስታወት ሲረግፍ አንድ የፖሊስ መኮንን ላይ ምራቅ መተፋቱ ተሰምቷል። የሙጋቤ ልጅ የቀረበበትን ክስ አጣጥሎ ከደሙ ንፁሕ ነኝ ይላል። አሁን ከእሥር ተለቆ ክሱን በድርድር ለመፍታት እየጣረም እንደሆነ ተነግሯል። ፖሊስ በትዊተር ገፁ እንደገለጠው የሮበርት ሙጋቤ ልጅ ጓደኛ የሆነው ሲንዲሶ ንካታዞ ያቀረበውን ቅሬታ ተከትሎ ነው ፖሊስ ወደ ሥፍራው ያቀናው። በድግሱ ላይ የደረሰው የንብረት ውድመት በገንዘብ ሲሰላ 12 ሺህ ዶላር አካባቢ ሊደርስ እንደሚችል ፖሊስ…
Read More
በወልቂጤ ግድያ የፈጸሙ የፀጥታ ኃይሎች በሕግ ይጠየቁ በሚል ነዋሪዎች አድማ መቱ

በወልቂጤ ግድያ የፈጸሙ የፀጥታ ኃይሎች በሕግ ይጠየቁ በሚል ነዋሪዎች አድማ መቱ

በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የውሃ አቅርቦት ችግር እንዲፈታ እና የውሃ ጥያቄያቸውን ለማቅረብ አደባባይ በወጡ ሰልፈኞች ላይ የተኮሱ የፀጥታ ኃይሎች ለፍርድ እንዲቀርቡ በመጠየቅ ከቤት ያለመውጣት አድማ መምታታቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ። ከቤት ያለመውጣት አድማው ከተጀመረ ቀናት መቆጠራቸውን የተናገሩት ነዋሪዎች የከተማዋ እንቅስቃሴም ሙሉ በሙሉ ተገድቧል ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። በከተማዋ ለወራት የተቋረጠው የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር እንዲፈታ ለመጠየቅ ባለፈው ሳምንት ጄሪካን ይዘው አደባባይ በወጡ ሰልፈኞች ላይ የፀጥታ ኃይሎች በከፈቱት ተኩስ ቢያንስ ሦስት ሰዎች መገደላቸውን እና ቢያንስ 30 ሰዎች የአካል ጉዳት መድረሱን ነዋሪዎች እና ኢሰመኮ ማስታወቃቸው ይታወሳል። በከተማዋ ትራንስፖርት፣ የባንክ አገልግሎት፣ የመገበያያ መደብሮችም ሆነ የትኞቹም የመንግሥት ተቋማት ተዘግተው ከተማዋ ጭር ብላ መሰንበቷን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ሰኞ ምሽት…
Read More
ኤሪክ ቴን ሃግ፡ የማንችስተር ዩናይትድ ‘ለውጥ ሐዋርያ’

ኤሪክ ቴን ሃግ፡ የማንችስተር ዩናይትድ ‘ለውጥ ሐዋርያ’

ግዙፉ የለንደኑ ዌምብሊ ስታድዬም 90 ደቂቃ ሞልቷል የሚል ምልክት ሲያሳይ የዩናይትድ ደጋፊዎች በኩራት ስካርፋቸውን ወደሰማይ ሰቅለው አውለበለቡ። ቀያዮቹ ሰይጣኖችና ደጋፊዎቻቸው ይህን ስሜት ካጣጣሙ ዓመታት ተቆጥረዋል። ደጋፊዎች ፊሽካው ከመነፋቱ በፊት ድላቸውን ሲያጣጥሙ፤ ይህን ለውጥ የሾፈረው ግለሰብ የአሠልጣኞች መቆሚያ ሥፍራ ላይ ሆኖ ሁኔታውን በጥሞና ይከታተላል። ዩናይትድ ለመጨረሻ ጊዜ ዋንጫ ያነሳው በ2017 የአውሮፓ ሊግ ፍፃሜ ነው። ዩናይትዶች ዋንጫውን እንዳነሱ አውቀውታል። የመጨረሻዎች ሽራፊ ደቂቃዎች ያስጨነቋቸው አይመስሉም። በመጀመሪያው አጋማሽ በስድስት ደቂቃዎች ልዩነት አከታትለው ያስቆጠሯቸው ሁለት ጎሎችን አስጠብቀው መውጣት ብቻ ነው የሚጠበቅባቸው። ምንም እንኳ በሁለተኛው አጋማሽ ኒውካስል ዩናይትድ ተነቃቅቶ ቢመጣም ኳስና መረብን ሊያገናኝ አልቻለም። ኤሪክ ቴን ሃግ በዩናይትድ መንደር ለውጥ እያመጣ ነው ብሎ በድፍረት መናገር ይቻላል።…
Read More
ከ18 ወራት በኋላ በሚካሄደው የፓሪስ ኦሊምፒክ 40 አገራት ያህል አድማ ሊመቱ ይችላሉ ተባለ

ከ18 ወራት በኋላ በሚካሄደው የፓሪስ ኦሊምፒክ 40 አገራት ያህል አድማ ሊመቱ ይችላሉ ተባለ

ከዓመት ከስድስት ወር በኋላ የሚካሄደውን የፓሪስ ኦሊምፒክ እስከ 40 አገራት ያክል አድማ ሊመቱ እንደሚችሉ ፖላንድ አስጠነቀቀች። የፖላንድ የስፖርት እና ቱሪዝም ሚኒስትር ካሚል ቦርትኒዙክ የፓሪስ ኦሊምፒክ ትርጉም አልባ ሊሆን ይችላል ብለዋል። ይህ የሚስትሩ አስተያየት የተሰማው ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ በፓሪሱ 2024 ኦሊምፒክ የሩሲያ እና ቤላሩስ ዜጋ አትሌቶች እንዲሳተፉ ለመፍቀድ ማቀዱን ፖላንድ፣ ሊቱኒያ፣ ኢስቶኒያ እና ላትቪያ በጋራ መቃወማቸውን ተከትሎ ነው። ዩክሬን የሁለቱ አገራት አትሌቶች የሚሳተፉ ከሆነ በውድድሩ አልገኝም ብላለች። የኦሊምፒክ ኮሚቴው ግን በውድድሩ ላይ አድማ ማድረግ ትርፉ “አትሌቶችን መቅጣት ብቻ ነው” ብሏል። የፖላንድ የስፖርት እና የቱሪዝም ሚንስትሩ የዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ ከሳምንት በኋላ ከሚያደርገው ስብሰባ በፊት ግሬት ብሪቴን፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና ካናዳን…
Read More
የኳታሩ ሼክ ጃሲም ማንችስተር ዩናይትድን ለመግዛት መዘጋጀታቸውን አስታወቁ

የኳታሩ ሼክ ጃሲም ማንችስተር ዩናይትድን ለመግዛት መዘጋጀታቸውን አስታወቁ

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጉልህ ታሪክ ያለው እና በዘንድሮው የውድድር ዘመን ሦስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማንችስተር ዩናይትድን ለመግዛት ባለሃብቶች ጥያቄያ አቅርበዋል። ከኳታር ትልልቅ ባንኮች የአንደኛው ሊቀ መንበር የሆኑት ሼክ ጃስሚ ቢን ሃማድ አል ታኒ ፋውንዴሽናቸው ማንችስተር ዩናይትድን ለመግዛት ጥያቄ ማቅረቡን አረጋግጠዋል። ቢቢሲ መረዳት እንደቻለው የሰር ጂም ራትክሊፍ ንብረት የሆነው ኢኒዎስም ማንችስተር ዩናይትድን ለመግዛት ፍላጎት እንዳለው አሳውቋል። ቢሊዮነሩ ራትክሊፍ ማንችስተር ዩናይትድን የመግዛት ፍላጎት እንዳላቸው ቀድመው አሳውቀው ነበር። በ2005 (እአአ) ማንችስተር ዩናይትድን የገዙት የግሌዘር ቤተሰቦች “ስትራቴጅክ አማራጮችን መፈለግ” በሚል ክለቡን ለመሸጥ አስበዋል። የኳታሩ ሼክ ጃሲም ክለቡን ወደ ቀድሞ ክብሩ የመመለስ ዕቅድ አለን በማለት ቡድኑን ቢገዙ ሊያደርጉ ያሰቡትን ገልጸዋል። የእግር ኳስ ቡድኑን ማጠናከር፣ የልምምድ…
Read More
በአፍሪካ የስፖርት ውድድሮች ላይ ዋነኛ አወዛጋቢ ጉዳይ የሆነው የዕድሜ ማጭበርበር

በአፍሪካ የስፖርት ውድድሮች ላይ ዋነኛ አወዛጋቢ ጉዳይ የሆነው የዕድሜ ማጭበርበር

ለዓመታት በአፍሪካ ስፖርት ላይ ጥቁር ጥላውን እንዳጠላ ነው። በቅርቡ በተካሄደው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ላይ የችግሩ ስፋት ታይቷል። የስፖርተኞች የዕድሜ ጉዳይ። ካሜሩን ባዘጋጀችው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ተሳታፊ ከነበሩት አገራት መካከል አንዷ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ነበረች። ነገር ግን ከጨዋታው ጅማሬ በፊት ከውድድሩ እንድትሰረዝ ተደርጓል። ምክንያቱ ደግሞ ለውድድሩ ከተላኩት ተጫዋቾች መካከል 25ቱ ዕድሜያቸው ከ17 ዓመት በላይ መሆናቸውን የኤምአርአይ ምርመራ በማሳየቱ ነው። ከኮንጎ በተጨማሪ ቻድ እንዲሁ ተጫዋቾቿን ካሜሩን ከላከች በኋላ ከውድድሩ ተሰርዛለች። የካሜሮን እግር ኳስ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ኤቶ የኤምአርአይ ምርመራ እንዲደረግ ካዘዘ በኋላ፣ ቻድ ለውድድሩ ካቀረበቻቸው ተጫዋቾች መካከል 30ዎቹ የዕድሜ ገደቡን አልፈዋል። በመላው ዓለም የእግር ኳስ ፌዴሬሽኖችን የሚያማክሩት…
Read More
ደቡብ ሱዳን ለዓለም የቅርጫት ኳስ ዋንጫ በመጀመሪያ ሙከራዋ በማለፍ ታሪክ ሰራች

ደቡብ ሱዳን ለዓለም የቅርጫት ኳስ ዋንጫ በመጀመሪያ ሙከራዋ በማለፍ ታሪክ ሰራች

የደቡብ ሱዳን የወንዶች የቅርጫት ኳስ ብሔራዊ ቡድን ለመጀመሪያ ጊዜ በተሳተፈበት ማጣሪያው በዚህ ዓመት በሚካሄደው የዓለም ቅርጫት ኳስ ውድድር ለመሳተፍ ማለፍ በመቻሉ ታሪክ ሰራ። የደቡብ ሱዳን የቅርጫት ኳስ ቡድን በአፍሪካ የማጣሪያ ውድድር ውስጥ ሲሳተፍ የመጀመሪያው ቢሆንም ወደ ታላቁ ውድድር በመጀመሪያ ሙከራው በማለፉ በአፍሪካ የመጀመሪያው ሆኗል። ‘ብራይት ስታር’ እየተባለ የሚጠራው ቡድኑ በግብፅ አሌክሳንድሪያ በተደረገው ውድድር ሴኔጋልን 83 ለ 75 በመርታት በሚቀጥለው ነሐሴ በሚጀመረው እና ኢንዶኖኔዢያ፣ ጃፓን እና ፊሊፒንስ በጣምራ በሚያዘጋጁት የዓለም ቅርጫት ኳስ ዋንጫ እንደሚሳተፍ አረጋግጧል። በውድድሩ አፍሪካ በአምስት ብሔራዊ ብድን የምትወከል ሲሆን፣ አይቮሪ ኮስትም ቀደም ብላ ማለፏን አረጋግጣለች። እንደአውሮፓውያኑ የዘመን ስሌት በ2011 ከሱዳን ተለይታ ነጻ አገር ሆና የተመሠረተችው ደቡብ ሱዳን 11.5…
Read More
አንጋፋው ብስክሌተኛ ገረመው ደንቦባ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አንጋፋው ብስክሌተኛ ገረመው ደንቦባ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

በኦሊምፒክ መድረክ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ለመጀመሪያ ጊዜ በማውለብለብ ቀዳሚ የነበረው ብስክሌተኛ ገረመው ደንቦባ ባደረበት ሕመም ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። የብስክሌት ስፖርተኛው ገረመው ደንቦባ በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በትናንትናው ዕለት በ90 ዓመቱ ሕይወቱ ማለፉን ቤተሰቦቹ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1956 ለመጀመሪያ ጊዜ በአውስትራሊያ ሜልቦርን ከተማ በተካሄደው የኦሊምፒክ ውድድር ስትካፈል ከተሳተፉ ብስክሌተኞች ገረመው ደንቦባ አንዱ ነበር። ብስክሌተኛ ገረመው ደንቦባ በበርካታ የብስክሌት ውድድሮች ተሳትፎ ከ26 በላይ ዋንጫዎችን እና ከ32 በላይ ሜዳሊያዎችን ተሸልሟል። አትሌቱ በስፖርቱ ዘርፍ ላበረከተው ጉልህ አስተዋፅኦ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሚያዘጋጀው የኢቢሲ ስፖርት አዋርድ 4ኛው የኢቢሲ-ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስፖርት ሽልማት የሕይወት ዘመን ተሸላሚ አትሌት ነበር። ገረመው ደንቦባ ታኅሣሥ 7 ቀን 1925 ዓ.ም በአዲስ…
Read More
ባሏን የገደለችው ዝነኛዋ አትሌት ጉዳይ

ባሏን የገደለችው ዝነኛዋ አትሌት ጉዳይ

አትሌት በሱ ሳዶ ከሁለት ወንድሞቿ እና ከሌሎች ሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በመሆን ባለቤቷን በመግደል ወንጀል ተከሳ ድርጊቱን መፈጸሟ በመረጋገጡ የእድሜ ልክ እስራት ተፈረደባት። በቅርበት የሚያውቋቸው የአዳማ አትሌቲክስ ክለብ አሰልጣኝ ሐብታሙ ግርማ ስለ ግድያው ሲናገሩ “እኔ በጣም ነው ያዘንኩት፤ በእርሱ ሞትም በጣም አዝኛለሁ። የእርሷም እስር ከሞት የማይተናነስ በመሆኑ እና አገሪቱም እንዲህ ዓይነት ሰው በማጣቷ በጣም ነው ያዘንኩት” ብለዋል። የአትሌት በሱ ሳዶ የቀድሞ አሰልጣኝ ስለ ሁኔታ ሲናገሩ የተፈጸመውን ወንጀል አምነው መቀበል እንዳዳገታቸው “እኔ አሁን ራሱ ይሄ ነገር እንዴት አንደተፈጠረ ሊገባኝ አልቻለም” ሲሉ ግራ መጋባታቸውን ገልጸዋል። የመካከለኛ እና የረዥም ርቀት ሯጯ አትሌት በሱ ሳዶ እንዲሁም አብሯት የነበረው ወንድሟ ከባለቤቷ ግድያ ጋር በተያያዘ ጥፋተኛ ሆነው…
Read More