መነሻ ገፅ

በደቡብ አፍሪካ ሰባት ኢትዮጵያዊያን መገደላቸው ተገለጸ

በደቡብ አፍሪካ ሰባት ኢትዮጵያዊያን መገደላቸው ተገለጸ

‎በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሀገሪቱ ባጋጠመው ቀውስ ምክንያት መጎዳታቸውን ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም በደርባን አከባቢ' ማርች ቱ ማርች ' በተባለ ስደተኛ ጠል አማጺ ቡድን ተደጋጋሚ ጥቃቶች በአጠቃላይ ስደተኞች ላይ ይፈፀሙ እንደነበር ነዋሪዎቹ ገልጸዋል። ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን በጁሀንስበርግ አካባቢ በኢትዮጵያውያን ላይ ያነጣጠረ ተደጋጋሚ ጥቃት እየተፈፀመ መሆኑን ተናግረዋል።‎‎ካሳለፍነው መጋቢት ወር አጋማሽ ጀምሮ በተከታታይ ቀናት 2 ለረጅም ዓመታት በሀገሪቱ የኖሩና ሃብት ያፈሩ አቶ ወንድሜነህ አየለ እና አብረሃም ይመር የተባሉ ኢትዮጵያውያን በጁሀንስበርግ ጂፒ ስትሬት ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በ16 እና በ3 ጥይት ተደብድበው መገደላቸው ተገልጿል።‎‎በደቡብ አፍሪካ ያሉ ኢትዮጵያውያኑ አክለውም " ሁለቱም ግለሰቦች የኢትዮጵያውያን አስተባባሪና በኢትዮጵያና በደቡብ አፍሪካም ትልልቅ ፎቆች ያሏቸው የተከበሩ ባለሃብቶች ነበሩ " ብለዋል።…
Read More
ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚሄዱ ሰዎች እስከ አንድ ሚሊዮን ብር እንዲያሲዙ የሚያስገድድ መመሪያ ተዘጋጀ

ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚሄዱ ሰዎች እስከ አንድ ሚሊዮን ብር እንዲያሲዙ የሚያስገድድ መመሪያ ተዘጋጀ

የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ወደ ውጭ አገር ሄደው ለሚታከሙ ዜጎች ጥራት ያለው፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ክብራቸውን የሚመጥን የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል ያለውን "የውጭ አገር የሕክምና አገልግሎት ቅብብሎሽ ሥርዓት ማስፈፀሚያ መመሪያ ቁጥር 1128/2018" አውጥቷል። ይህ አዲስ መመሪያ በዋነኝነት የታካሚዎችን እንግልት ለመቀነስ፣ የሚታዩ የአሰራር ክፍተቶችን ለመሙላት እና በሕክምና ስም የሚከናወኑ ሕገ-ወጥ ተግባራትን ለመቆጣጠር ታስቦ የተዘጋጀ  መሆኑን አስታውቋል። መመሪያው በጤና አገልግሎት አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 1362/2017 መሰረት የወጣ ሲሆን፣ ከሕክምና ቦርድ አሰራር ጀምሮ እስከ ወኪል ተቋማት የብቃት ማረጋገጫ ድረስ ያሉ ሂደቶችን በዝርዝር ይደነግጋል። በመመሪያው መሰረት አንድ ታካሚ ወደ ውጭ አገር ሄዶ እንዲታከም የሚፈቀድለት አራት ዋና ዋና መስፈርቶችን ሲሟሉ እንደሆነ ያስገድዳል። ከመስፈርቶች መካከልም የሚፈለገው የሕክምና ዓይነት…
Read More
ዶክተር ሚዛኔ አባተ የኢሰመኮ ምክትል ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ

ዶክተር ሚዛኔ አባተ የኢሰመኮ ምክትል ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተጓደሉ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር የኃላፊነት ቦታዎች ላይ የቀረቡ አራት ዕጩዎችን ሹመት አጽድቋል። ዶ/ር ሚዛኔ አንጋፋ የሰብአዊ መብቶች ምሁር እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብአዊ መብቶች ሕግ ረዳት ፕሮፌሰር ሲሆኑ፤ በሰብአዊ መብቶች ክትትል፣ በተቋማዊ ሪፎርም እና በሕግ ትምህርት ረገድ ሰፊ ልምድ አላቸው። በኢሰመኮ ውስጥ በተለያዩ ከፍተኛ የአመራር ኃላፊነቶች ያገለገሉ ሲሆን፣ በቅርቡም የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር  ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ በመሆን በፖሊሲ ልማት እና በተቋማዊ ግንባታ ረገድ ጉልህ አስተዋጽዖ አበርክተዋል። አቶ በዳሳ ለሜሳ ከበደ የሰብአዊ መብቶች ትምህርት እና ሥልጠና ኮሚሽነር በመሆን ተሹመዋል። አቶ በዳሳ በሰብአዊ መብቶች ክትትል፣ በምርመራ እና በተቋማዊ አመራር ሰፊ ልምድ ያላቸው አንጋፋ ባለሙያ መሆቸው ተገልጿል። በቅርቡ በኢሰመኮ የክትትል…
Read More
ከ3 ሺህ በላይ ሰዎች ፓስፖርት በህገወጥ መልኩ ለማግኘት ሲሞክሩ መታሰራቸው ተገለጸ

ከ3 ሺህ በላይ ሰዎች ፓስፖርት በህገወጥ መልኩ ለማግኘት ሲሞክሩ መታሰራቸው ተገለጸ

ባለፋት ዘጠኝ ወራት በህገ ወጥ መንገድ የፓስፓርት አግልግሎት ለማግኘት የሞከሩ ከ3 ሺህ በላይ ሰዎች በቁጥጥር ስር ዉለዋል ተብሏል። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በ2018 በጀት አመት ዘጠኝ ወራት ያከናወናቸውን አገልግሎት አፈፃፀም በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት እንደተናገሩት ባለፋት ዘጠኝ ወራት 3 ሺህ 6 መቶ 38 ግለሰቦች በህገ ወጥ መንገድ የፓስፓርት አግልግሎት ለማግኘት የተጭበረበረ ሰነድ ይዘው ሲንቀሳቀሱ ነበር። ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ  300 የውጭ ዜጎች እና 3ሺህ3 መቶ 38 ኢትዮጵያውያን በህገ ወጥ መንገድ አገልግሎት ለማግኘት የተጭበረበረ ሰነድ ይዞው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ እና ትክክለኛ ያልሆነ የዜግነት ማስረጃ ይዘዉ የተገኙ መሆናቸው ተጠቁሟል። በዚህም መሰረት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጋቸውን…
Read More
ከ300 በላይ የአውሮፓ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መሰማራታቸው ተገለጸ

ከ300 በላይ የአውሮፓ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መሰማራታቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ህብረት የቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ሲሆን ነገ ፍጻሜውን ያገኛል ተብሏል። የኢትዮጵያን እና አውሮፓን ንግድ እና ኢንቨስትመንት ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀው ይህ ጉባኤ መሪዎች፣ የንግድ አማካሪዎች፣ የኩባንያ ባለቤቶች እና ሌሎችም ተገኝተውበታል፡፡ በጉባኤው ላይ የተገኙት የአውሮፓ ህብረት የአለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽር ጆሴፍ ሲኬላ እንዳሉት 300 የሚጠጉ የአውሮፓ ሀገራት ኩባንያዎች በተለያዩ ዘርፎች በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ በኢንቨስትመንት ላይ ናቸው ብለዋል። በሌላ በኩል የአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ የንግድ ቀጠናን ተግባራዊት ለማፍጠን የሚያግዝ 1.2 ቢሊዮን ዮሮ ድጋፍ ስምምነትም በፎረሙ ላይ ተፈርሟል። ከዚህ በተጨማሪም የአውሮፓ ህብረት በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት አቋርጦት የነበረውን የበጀት ድጋፍ ዳግም መጀመሩ ተገልጿል። በዚህም ህበረቱ ለኢትዮጵያ መንግስት የበጀት ድጋፍ 140 ሚሊዮን…
Read More
የቴዲ አፍሮ አዲስ አልበም “ኢቶሪካ” ከወዲሁ አነጋጋሪነቱ ቀጥሏል

የቴዲ አፍሮ አዲስ አልበም “ኢቶሪካ” ከወዲሁ አነጋጋሪነቱ ቀጥሏል

ከስምንት ዓመት ቆይታ በኋላ አምስተኛ አልበሙን እንደሚለቅ ያሳወቀው ድምጻዊ ቴድሮስ ካሳሁን ወይም ቴዲ አፍሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ትኩረት ስቧል። የፊታችን ሐሙስ ሚሚያዝያ 8፣2018 "ኢቶሪካ" የተሰኘውን የሙዚቃ አልበም ለአድማጮች እንደሚያደርስ ካሳወቀ በኋላ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ዋነኛው መነጋገሪያ ሆኗል። ድምጻዊው ስለ አዲሱ አልበሙ ሊሰጠው ያሰበው ጋዜጣዊ መግለጫ በመንግስት ተጽዕኖ ምክንያት ማካሄድ እንዳልቻለም ተገልጿል። ይህን ተከትሎም ብዙዎች ለድምጻዊው ድጋፋቸው በማሳየት ላይ ሲሆኑ ታዋቂ አርቲስቶች እና የቀድሞ ፖለቲከኞች ድጋፋቸውን ለድምጻዊ ቴድሮስ እያሳዩ ይገኛሉ። ድምጻዊ ቬሮኒክል አዳነ በፌስቡክ ገጿ ላይ ባጋራችው ጽሁፍ "በእውቀትም፣ ዝናን በመቆጣጠርም፣ አለው አለው ባለማለትም፣ በድምፅም፣ ፍቅርን በመስበክም፣ ለህዝብ በመቆምም፣ ሀገር በመውደድም፣ ለተጎዳ በመድረስም፣ ሀይማኖትን በማክበርም፣ ለቤተሰብ ቅድምያ በመስጠትም፣ ታሪክን በማወቅም፣ እግዚአብሔርን…
Read More
በነጻ የንግድ ቀጠናዎች ያሉ ነጋዴዎች ከግብር ነጻ ሆነው እንዲሰሩ ተወሰነ

በነጻ የንግድ ቀጠናዎች ያሉ ነጋዴዎች ከግብር ነጻ ሆነው እንዲሰሩ ተወሰነ

በነጻ የንግድ ቀጠናዎች ውስጥ ግብአቶችን እና ምርቶችን ለገበያ በማቅረብ ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶች ከገቢ ግብር ነጻ እንዲሆኑ ተወሰነ:: የገንዘብ ሚኒስቴር ለገቢዎች ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ እንዳስታወቀው በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ልማት በሚፈለገው መጠን እንዳያድግ ምክንያት ከሆኑት መካከል የካፒታል እጥረት፤ የግብአት አቅርቦት ችግር  እና የባለሙያ እጥረት በዋንኛነት ምክንያት አስቀምጧል፡፡ እነዚህን ችግሮች ደረጃ በደረጃ በማቃለል የአገር ውስጥ ኢንዱስትሪ ልማትን  ማሳደግ አእንደሚገባ በደብዳቤው ላይ ጠቅሷል፡፡ ግብአቶች እና ሌሎችም ምርቶች በበቂ መጠን ለገበያ እንዲቀርቡ ለማድረግ አስመጪዎች ምርቱን ለገበያ ከማቅረባቸው በፊት የሚከፍሉት ቀረጥ እና ታክስ ውስን የሆነውን ካፒታላቸውን በመያዝ ረገድ የሚያሳድረባቸውን ጫና ማቃለል እንደሚያስፈልግ አስታውቋል። አስመጪዎች  ግብቶችን  እና ምርቶችን ቀረጥ እና ታክስ ሳይከፍሉ ወደ አገር ውስጥ አስገብተው ለግብአቱ…
Read More
ኢትዮጵያዊያንን ለስራ ወደ ካናዳ መላክ የሚያስችል ስምምነት ተፈጸመ

ኢትዮጵያዊያንን ለስራ ወደ ካናዳ መላክ የሚያስችል ስምምነት ተፈጸመ

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በካናዳ ከሚገኘው ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል (FFI) ጋር በክህሎት ልማትና ሥራ ዕድል ፈጠራ መስኩ በጋራ መስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል። ስምምነቱ ለኢትዮጵያውያን ወጣቶች የክህሎት ልማትን ለማጠናከር፣ የሥራ ዕድል ለመፍጠር እና ዓለም አቀፍ የሥራ ዕድሎችን ለማመቻቸት ዕድል የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል። በመርሃ ግብሩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል፣ ከኢንቨስትመንቶች ሁሉ ትልቁ ኢንቨስትመንት የሰው ኃይል ልማት ላይ የሚደረግ ኢንቨስትመንት ነው፡፡ ስምምነቱ የሥራ ዕድል ከማመቻቸት ባሻገር ወጣቶችን በስልጠና ማብቃት ላይ ያተኮረ በመሆነ በኢትዮጵያ ወጣቶች ላይ የሚደረግ የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት ነው ብለዋል። ይህም የዜጎችን እምቅ አቅም በመፍጠር ለዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ ከማቅረብ ባለፈ አጠቃላይ የሰሪ ኃይላችንን የሚያጠናክር እንደሆነም…
Read More
አንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

አንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

አንጋፋዋ የኢትዮጵያ ዲፕሎማት አምባሳደር  ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል። አምባሳደር ቆንጂት የውጭ ጉዳይ ሚንስቴርን በ1950ዎቹ በለጋ እድሜያቸው ተቀላቅለው ከዴስክ ኦፊሰርነት እስከ ከፍተኛ አመራርነት አገልግለዋል። አምባሳደር ቆንጂት ከዮዲት እምሩ በመቀጠል በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደርም ናቸው። አምባሳደሯ በኦቶዋ፣ ካይሮ፣ ቴል አቪቭና ቬይና በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን፤ በአፍሪካ ህብረትና በተባባሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽንም ቋሚ መልዕክተኛ በመሆን ሰርተዋል። ከሰኔ 2009 እስከ መስከረም 2011ዓ.ም ደግሞ ኢጋድ በመራው የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት ላይም ልዩ አማካሪ ነበሩ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአምባሳደር ቆንጂት ሕልፈትን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ  ኢትዮጵያ ዲፕሎማቷን እንዳጣች እና ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማው…
Read More
ኢትዮጵያ የካንሰር መድሀኒቶችን በሀገር ውስጥ ለማምረት በዝግጅት ላይ ናት ተባለ

ኢትዮጵያ የካንሰር መድሀኒቶችን በሀገር ውስጥ ለማምረት በዝግጅት ላይ ናት ተባለ

ኢትዮጵያ ለካንሰር ህመምተኞችን ለማከም የሚውሉ መድኃኒቶችን ሙሉ በሙሉ ከውጪ በማስገባት ላይ ትገኛለች። ይሁንና እነዚህን መድኃኒቶች በሀገር ውስጥ ለማምረት የአዋጭነት ጥናት በማድረግ ላይ መሆኑ ተገልጿል። ባለሀብቶች በተለያዩ ዘርፎች የካንሰር መድኃኒቶችን በሀገር ውስጥ እንዲያመርቱ የሚያስችል ፕሮጀክት በቂልንጦ ፋርማሲዩቲካል ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ ገብተው በፕሮጀክት ደረጃ ይዘው  ስራ መጀመራቸው ተገልጿል። በቅርብ ጊዜ  እነዚህን ፕሮጀክቶች በመደገፍ  የፕሮጀክት ጊዜያቸውን አጠናቀው  ወደ ምርት እንዲገቡ የአርማሆር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት ድጋፍ እንደሚያደርግ  በአርማሆር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት  የፋርማሲዩቲካል ኢንዱስትሪ ልማት  ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር መሳይ ወ/ማርያም ተናግረዋል። መድኃኒቶች በሀገር ውስጥ መመረት ከመጀመሩ በፊት በሀገር ውስጥ ቢመረቱ ነው ወይስ ከውጪ ቢገቡ የተሻለ የሚሆነው የሚለውን ጥናት ያማከለ እንደሚሆንም ተመራማሪው አክለዋል። ይሁንና በሀገር ውስጥ መመረት ሲጀምሩ  ከውጪ  የሚገቡትን…
Read More