አሜሪካ አንድ ዜጋዋ ሱዳን ውስጥ እንደተገደለባት ገልጸች

አንድ የአሜሪካ ዜጋ ሱዳን ውስጥ እየተካሄደ ባለው ውጊያ መገደሉ ተሰምቷል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለፎክስ ኒውስ በሰጠው ቃል ፤ በሱዳን አንድ አሜሪካዊ ዜጋ መሞቱን አረጋግጧል።

መስሪያ ቤቱ ፤ ከሟች ቤተሰብ ጋር እየተገናኘ መሆኑንና በደረሰባቸው ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል።

“በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ለቤተሰብ ካለን አክብሮት የተነሳ ምንም የምንጨምረው ነገር የለም ” ሲልም ስለ ሟች ዝርዝር መረጃ ይፋ ከማድረግ ተቆጥቧል።

በሌላ በኩል ፤ የአሜሪካ መከላከያ ጦር በአፍሪካ ኮማንድ በኩል በሱዳን ያለውን ሁኔታ እየተከታተለ መሆኑን አሳውቋል።

አሜሪካ በሱዳን ያሉ ዜጎቿን ደህንነት ለማረጋገጥ ወደ ጅቡቲ ተጨማሪ ወታደሮችን ለመላክ እያሰበች መሆኗንም አስታውቃለች።

የአሜሪካ ጦር ፤ በካርቱም የሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲ ሰራተኞችን እና ዜጎችን ለማስወጣት የሚያስችለውን ተልዕኮ ለመፈፀም ተጨማሪ ኃይሎቹን ጅቡቲ ለማስቀመጥ ዝግጅት እያደረገ እንደሆነ ተሰምቷል።

By New admin

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *